Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Wednesday, January 21, 2015

እንደ አስቴር በዳኔ ያልሆኑ አርቲስቶችን ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ወቀሱ


<<ዝም ብላችሁ ጥሩ ነገር ብቻ ብትናገሩ አንሰማችሁም፤ እንደውም አጭበርባሪ ነው የምንላችሁ>> ሲሉ ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል -አርቲስቶችን ተናገሩ።

ጥር ፲፪(አስራ ሁለት ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ደብረጽዮን- ከአርቲስቶች ጋር ባደረጉት ዝግ ስበሰባ የተናገሩት ነገር ተቀርጾ በይፋ በማህበራዊ ሚዲያዎች የተለቀቀ ሲሆን፤ በንግግራቸው አርቲስቶችን ሲመክሩና፣ ሲያባብሉ እና ሲገስጹ ተሰምተዋል።
<<በፌስ ቡክ የሚነገረንን ነገር እንሰማለን፤አርቲስቶች ሆዳሞች እንደምትባሉ እናውቃለን!>> ያሉት ዶክተር ደብረጽዮን፤ <<መለስን ሳይቀር የሚሳደቡ አሉ፤ መለስን ብቻ ሳይሆን ሁላችንንም ሲሰድቡን አይተናል>> ብለዋል።
<<እናንተም የፈለጋችሁትን ነገር ንገሩን፤ ስድብም ከፈለጋችሁ ህሊናችሁ ከፈቀደ ስደቡን>> በማለት ለአርቲስቶቹ የተናገሩት ዶክተር ደብረጽዮን፤ <<ዝም ብላችሁ ጥሩ ጥሩ ነገር ብቻ ብትናገሩን አንሰማችሁም፤እንደውም አጭበርባሪ ነው የምንላችሁ>>ብለዋቸዋል።
አክለውም፦<< እናንተ ባትነግሩንም ችግር እንዳለብን እኛ እናውቃለን፤ዝም ብሎ የሚቆልለንን ፊት ለፊቱ ባንናገረውም፤ ዞር ስንል ግን አጭበርባሪ ነው ማለታችን አይቀርም>> ሲሉ ገስጸዋቸዋል።
ህወሀት የተመሰረተበትን 40ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ወደ ደደቢት አቅንተው የነበሩ አርቲስቶች በሙሉ ህወሀትን ሲያወድሱና ሲያሞካሹ፤ አርቲስት አስቴር በዳኔ ብቻ ጠንካራና ሞጋች ጥያቄ ማንሳቷ ይታወቃል።
አርቲስቷ ከ ኢሳት ጋር ባደረገችው ቃለ-ምልልስ ፦ያን ጥያቄ ካነሳች በሁዋላ ባለስልጣናቱ ሲያበረታቱዋት፤ ሌሎቹ የሙያ አጋሮቿ ግን እርሷ ጋር ላለመታየት እንደሸሿት ገልጻለች።
በአርቲስቶች በደረሰባት መገለል የተከፋችው አስቴር በዳኔ፤ የሙያ ጓደኞቿ ያልሆኑን ከመሆን የአስመሳይነት ህይወት እንዲወጡ መክራለች።



No comments:

Post a Comment

wanted officials