ወኪላችን እንዳለው ታጣቂዎቹ፤ አርሶ አደሮችን በኃይልና በማን አለብኝነት አስነስተው ቦታውን ለማካለል ያደረጉትን ጥረት የአካባቢው ህዝብ ከዳር እስከዳር በመንቀሳቀስና ውጊያ ጭምር በመግጠም ነበር ያከሸፈው።በወቅቱ የታጣቂዎቹን እርምጃ ተከትሎ በተቀሰቀሰው ግጭት ከሁለቱም በኩል ጉዳት መድረሱ ታውቋል።
ውጥረቱ እስካሁን ያልበረደ ከመሆኑም ባሻገር የ አካባቢው ሕዝብ ከዳር እስከ ዳር እየተጠራራ ንብረቱን ለማስጠበቅ በአንድ ተሰባስቦ መዘጋጀቱ፤ ሌላ ዙር የከፋ ግጭት ይቀሰቀሳል የሚል ስጋት አሳደሯል።
No comments:
Post a Comment