Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Sunday, March 29, 2015

የኮሜዲያን ዳንኤል ቁንጮ ቀብር ስነስርዓት ተፈጸመ




ዳንኤል ቁንጮ ከእናቱ ወ/ሮ አስራት ሰቤ እና ከአባቱ ወልዴ ኪሮ በ1970ዓ.ም አዲስ አበባ 4ኪሎ – ፊት በር ተወለደ፡፡ አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በዳግማዊ ምኒሊክ ተማረ፡፡ ትያትር በተለያዩ ክበባት ተምሯል – ሰዓሊም ነበር፡፡

ዳ ኤል ቁንጮ – በተለያዩ ክለቦች በዲጄነት ሲያገለግል ከነዚህም ውስጥ ፒያዛ – በአካልፀ ሆቴል እና 22 ማዞሪያ – ሰገን ሆቴል ይጠቀሳሉ፡፡ ኮሜዲያን ዳኒ ቁንጮ በርካታ የኮሜዲ ሥራዎቹን አበርክቷል፡፡

እናቱ ወ/ሮ አስራት ሰቤ ልጃቸው በታመመበት ወቅት ወደ ሚዲያ ቀርበው ‹‹እባካቹ ልጄን አትርፉልኝ?›› ሲሉ ተማጽነው ነበር፡፡ ሐሙስ ዕለት ተክለሃይማኖት ሆስፒታል ለህክምና ገባ፡፡ ትላንት ቅዳሜ መጋቢት 19 ቀን 2007ዓ.ም በአደረበት ህመም በ37 ዓመቱ ያረፈው ዳን ኤል ቀብሩ – ዛሬ ከቀኑ 6፡00 ሰዓት በሳሊተ ምህረት ቤተ-ክርሲቲያን (ጉርድ ሾላ) ወዳጅ ዘመዶቹና የሙያ አጋሮቹ በተገኙበት ተፈጽሟል::

No comments:

Post a Comment

wanted officials