Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Friday, November 28, 2014

እስረኞችን ለመጠየቅ ቃሊቲ የሄዱ ሰዎች በቁጥጥር ሥር ከዋሉ በኋላ ተለቀቁ

በአንድነት ፓርቲ በቃሊቲ እና ቂሊንጦ የሚገኙ የህሊና እስረኞችን ለመየጠቅ ወደስፍራው ያመሩ ወደ 30 የሚገመቱ ሰዎች ቀትር ላይ በቃሊቲ በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ መለቀቃቸው ታወቀ፡፡
የአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆኑት አቶ አስራት አብርሃ ከ30 ደቂቃዎች በፊት በስልክ እንደነገሩኝ ከሆነ ‹‹እነእስክንድርንና አንዷለምን መጠየቅ አትችሉም፡፡ ተባልን ከዚያም ‹‹ለምን?›› ብለን ስንጠይቅ በዋናው በር በኩል ኃላፊውን አነጋግሩ የሚል መልስ ተሠጠን፡፡ እኛም ይህንን አምነን ሄድን፡፡ ስንደርስ በቁጥጥር ሥር ውላችኋል ብለውን ወደ 30 የምንገመት ሰዎችን መታወቂያችንን ከመዘገቡ በኋላ በአንድ ክፍል ውስጥ ለጊዜው እንገኛለን›› ብለውኝ ነበር፡፡ አሁን ባገኘሁት መረጃ መሰረት ደግሞ በኮንቴይነር ውስጥ ታግተው የነበሩት እስረኛ ጠያቂዎች ከበድ ያለ ፍተሻ ተደርጎላቸው ከቃሊቲ ግቢ እንዲወጡ ተደርጓል
a3a1a2

No comments:

Post a Comment

wanted officials