Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, May 27, 2014

የአቁአም መግለጫ ለምርቱ ገለባ መንግስታችን

ምርቱ ገለባ መንግስታችን
 በእኛ ሀገር በእምዬ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ምንም ሲሆን ምንም ሊደረግ ይችላል ሰው ለሞት ይችላል ሊታሰር ይችላል ምንም የሚገርም አይደለም ብዙ ልምድ አለን ይህ መንግስት እቺን ሀገር መግዛት ከጀመረ ወይም ቢደርግ ዘመን ጀምሮ ነፃ እናወጣለን ብለው ከተነሱበት ጊዜ ቢደረግ ዘመን መንግስት 17 ዓመት የነበረው የደም መፍሰስ የነበረው የሰው ልጅ ሰቆቃ ሀገሪቱን የጦር አውድማ ሆና በዛ መሀል ይቺ ሀገር ያተረፈችው የንፁሀን ደም ማፍሰስ ነው ወይም የበለፀጉ አገሮች የመሳሪያ ሽያጭ ማጣሪያ መጋዘን ተብሎም ተባልተውም የስንቱ ጀግና ወንድሞቻችን ሬሳ የአምራ ፊት ሆኖ ቀርቶል መነሻው ምንም ይሁን የሞት ግን የእኛው ወንድሞቻችን ናቸው ውጤቱም ሀገር መገንጠል ወደቡ አልባ ማድረግ ሁሉም ቢሆን ያ የነበረው ሮሮ በዛው ደረጃ የቀጠለበትን ሁኔታ ግን ስትመለከት ማነው ነፃ አውጪ ልዩነቱ በአደባባይና በስውር መሆኑ ነው በደርግ ዘመን መንግስት ወጣቱ ተለቅሞ ግዳጅ ወንድሙን ለመግደል ታጠቅ ይባላል በተመሳሳይ ለሚያነሳው ጥያቄ አብዩቱን በመቃወም ተብሎ በአደባባይ ይርሸን ነበር፡፡
 በአሁኑ ወቅት ደግሞ በተመሳሳይ ልማቱን በሚደናቀፍ ተብሎ አሻባሪ ይባላል ሰብአዊ መብቱን ባለማክበር የሰው ልጅ ስብእና በማይፈቅደው መልኩ ሲንገላታ ሲሞት ተመልክተናል በተለይ ለሀገር ይጠቅማል ተብሎ የሚገመተው የተማሪው የወጣት ኃይል በስደት ስሩን ለሀገር በመንቀል በከፍተኛ ደረጃ የተዋረድንበት ዘመን ነው ቢደረግ ዘ/መንግስት ስደቱ ሀገሪቱ ባለመረጋጋቱ ነው ጦርነት በመሆኑ ነው ብንል ግን በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ ደረጃ የሚሰደደውን ምን ምክንያት ይሰጠው መንግስት ??? ይህ ትውልዱ ሆነ ያትውልዱ ሁሉም አልቀረበትም ይመስለኛል ማን ነው የሚኖረው ማን ነው አኖኖሪ በሚል በንፈታው እንኳን ምስክርነት የሚሰጡት እነ ማን ናቸው ቢደንብ መፈተሸ አስፈላጊ ነው በጣም በደንብ 

በተለያየ ሶሻል ሚዲያ ይሁን በተለያየ የህዋህት ኢህደግ ልሳን የሆነው ኢትዮ ቴሌቨዥን አንዲ ሁለት ሶስትም በለው አራት በተለያየ የሬዲዮ ኘሮግራም ላይ በተመሳሳይ እነማን ናቸው???ይህንን አትኩረን መመልከት ከቻልን መልሱ ባቅሪያባችን ነው በጣም በቀላሉ መሰልና ተያያዥ ችግሮችን ሳይሰለቸው ተሸክሞ በዝምታ ቢጓዝም መፍትሔ ባለማግኘት ግንባር ቀደም የሰብአዊ መብት ረጋጭ ኢትዮጵያ ናት በማለት በመግለጫ ሁሌ በተለያየ የሰብአዊ መብት ድረጅቶች በማውጣት ቢቃወሙትም ደንዳናውና እና ጆሮውን በጥጥ የደፍነው ካሰረ ከገደለ ካሳደደ ከደርግ በአንድነት መንፈስ አውጥተው እስከመገንጠል ብለው የኢትዮጵያን ህዝቦች በአንድነት የመኖር መንፈስ ለማጥፋት ከፍተኛ የሆነ ሴራ ከሰራው ስራ የሚበልጥ በመሆኑም ይህንን ስርአት በመደገፍ ሲል አላማውን ሳይሆን ጥቅማ ጥቅሙን ወይም ለህሊና ሳይሆን ለሆዱ ተገዥ በመሆን ተምረናል የሚሉትን አስተምረናል የሚሉት በመማር ላይ ያሉትንም እረ ስንቱን አየነው በከፍተኛ ደረጃ በከፍተኛ ማዕረግ ተመርቀው ሳይማር ያስተማራቸውን ህዝብ ማገልገል ሲገባቸው የተነሱበትን አላማ ከሳቱ ከሀገር ሀብት ከሚቦጠቡጡ ባንዳዎች ጎን በመሰለፍ የህዝቡን ሆይታ አይቶ እንዳላየ በዝምታም ማለፍ ነገር ነው በተቃራኒው የተጎዳውን በመውቀስ ጉጂውን በማበረታታት አጀታችንን ሲያቅስሉት ኖረዋል ይህንንም በማስቀጠል በጎንደር በጎጃም በኦሮሚያ በትግራይ በአፈር በጋንቤላ ብቻ በሀገሪቱ አራቱም አቅጣጫ አሁንም ቢሆን የሆይታ ጎዞ እንደቀጠለ ነው በጣም ብዙ ደሞ ይፈሳል በጣም ደግሞ ብዙ ንፁሁን በእየ እስር ቤት ታጉረዋል በእውቀት ላይ መሠረት ያረጉ ሀገሪቱን አይደለም በአለም አቀፍ መደረክ በዲኘሎማሲ አመርቂ ውጤት ሊያመጡ የሚችሉ ብዙ ምሁራን ለህሊናቸው የኑሮ ውዴት ገቡ? እናውቃለን ይቺ ሀገር ለመኖር ምቹ አስመስሎ ኢቲቪ ቢያስኮመኩመንም እኛ በምንኖረው ምስክር ነን አልተመቸንም ብለን ብናወራ አላስተዳደርከንም አልቻልክም ብለን በሰላማዊ መንገዱ ብንጠይቀው ለጥያቄህ መልስ ሳይሆን ህይወትህን መንጠቅ የሆነው መንግስታችን ብዙ ምርት አሳይቶናል

 እኔ ግን ይህንን የሬሳ ምርት ስራው በማድረግ በጣም ብዙ ከሬሳ የማይሻሉ ተምረናል የሚሉ የሀገር ፍቅር አለን የሚሉ ምርቶችንም በተለያየ ወንበር ላይ ማስቀመጡን በመቀጠል ይህም 23 ዓመት ሞላው የተከፈለው መስዋትነት በተለያየ ጊዜ ወንድም በወንድሙ ላይ በመነሳት ጀብዱ በመፈጽምም አንድ ስርአት ወዴቆ ይኸው ሌላ ስርዓት መቷል በዚያ ሰዓት ህይወታቸው ያለፉ ወገኖች በጣም በሀዘኔ አዝኜ ክብር ለሰማዕታት ከእነ አላማቸው ትልቁ ጥያቄ ግን አላማቸው መንገድ ስቶ ከአስፓልት ወጥቶ የት እንደገባ አልታውቁም በተለያየ ጊዜ የተለያየ ምስክሮች ሰምተናል ሲያወሩ ሰምተናል በቻሉት ቋንቋ ሲናገሩ አላማቸውን ሲያወሩ “ህዝቡ እንዲያወርዱ እንደሰቅል” ያሉም አሉ ለአንዲት ኢትዮጵያ ብለው ያሉ አሉ ግን ችግሩ እነሱ አሁን በህይወት የሉም በትግል ያለቁት ሳይሆን ከተማ ከገቡ በኋላ የተገደሉም አሉ ለምን? እንዴት? በማን? ብዙ መሰል ጥያቄዎችን የሚያስነሱ ግን መልስ የሚሹ ጥያቄዎችን አሁን ባሉት የዛን ገዳይ ስርአት አስወግደናል ህግ በማርቀቅ ሪፊሪደም በማለት ኤርትራን ስትገነጠል ሀገራችን ወደብ አልባ ስትሆን ለህዝቡ የመምረጫ ወረቀት ላይ የተፃፈው ምን ተብሎ ነው ነፃነት/ባሪነት ይህ ማለት ኢትዮጵያን ሲመርጡ ባሪነት ኤተርትራን ሲመረጠ ነፃነት ስለዚህ በዛ ትግል በየምህነትና ለሀገር ሲሰሩ የነበሩትን አሁን በህይወት የሌሉበትን ሁኔታ ሳስብ ሳስብ በጣም በጣመ መልስ አጣለው ሰው በሁለት መንገድ ይጎዛል በተንኮል እና በንፁህ ወይም በየዋህነት በሴራው መንገድ የሄዱ አሸንፈው ይሆን እንዴ አዲስ አበባ 1983 ግንቦት 20 የገባው ብዬም አስባለው ንፁዋን የሉም ማለት አልችልም አበቃለት ተብሎ ስርዓቱ ተከፋፍሎ የተባሉ ጊዜ ግማሹ በእስር ግማሹ በሞት ተነጥለዋል ግን ግን የኤርትራ መገንጠል ፣የህዋህት መከፋፈል ፣የባለስልጣን በሙስና መጨ መላለቅ፣ የመካላከያ ሚኒስተር በአንድ እገዛ በጠቅላይ ሚኒስተር ስር መግባት፣ የአለመተማመን ምልክት ሰናይ ከህዝቡ ጀርባ የተደበቀ ስራ አለ የሚለውን ከፍተኛ ጥያቄ ያለው ጥራጣሬ??? በመቀጠል የሀይማኖት አለመረጋጋት በኦርቶዶክስም ሆነ የሙስሊም በውስጣቸው የመረጋጋት ስሜት አለመታየት የሙስሊሙ ማህበረሰቡ በሰላማዊ መንገድ የጠየቀው ጥያቄ ይህው ሁለት ዓመት በላይ ሆኖታል በተመሳሳይ የኦርቶዶክስ ሀይማኖት የሆነውን ማህበር ቅዱሳን የእነዚህ ሀይማኖቶች እንደ ባህር ወጀብ መናወጥ የሀገሪቱን የቀጣይ አቅጣጫ ወዴ እያመራ ነው በጣም ሊታሰብበት የሚገባ የብሔር ተንኮል ፓለቲካ እያመጣ ያለው መዘዝ የኑሮ ውድነት በሀገር የሚኖሩ አማሮች ዜጎች ከሀገር በመውጣት በሀሳቡም ሆነ የአካል የመንግስት ምርጫ ተኮር የልማት ስራዎች ለሀገር ሳይሆን ለወንበር በማሳብ የሚወስዳቸው እርምጃዎች በጣም የሚገርመው ሰው በሀገሩ መጠቀም ሲችል የፖለቲካ አስተሳሰቡ መሰረት ያደረገ የዜጎችን የዜግነት ጥያቄ በደረጃ በመከፋፈል ነዋሪ አኗኗሪ ተመልካ በዚህ የዘቀጠው መንግስታችን እኔ በእኔ እይታ በፊትም ይገደል ነበር አሁንም ይገደላል በ1997 የተጨፈጨፈ ኢትዮጵያን በአሁን ወቅት በተመሳሳይ የተማረውን ለሀገር ተስፋ የሚሆኑ የዩንቨርስቲ ተማሪዎች በመገደል ስራ ላይ የተጠመደው ህዋህት ኢህዴግ ለሀገር የሚበጅ ለቀጣይ ለዚች ሀገር ህልውና በሚያስብ መልኩ ብዙዋኑን የማያስደስት ብዙዋኑን ደግሞ የሚጎዳ ስራ በመስራት ከአዛውንት ፣ከወጣት፣ከሴት፣ ከወንድ፣ በህፃናት፣ በሀይማኖት አባቶች፣ ከኢትዮጵያ ህዝቡ የተጣላው ህዋት ኢህዴግ በደህንነት በመከላከያ እንዲሁም በፌዴራል ፓሊስ በመታገዝ ሲሰራ የከረመውን የዘረኝነት የክፋት ፓለቲካ የንፁዋንን ህይወት በማጥፋት በማፈናቀል በማሳደድ ይህው ምርቱ ገላባ ሆኖ ይገኛል በመሆኑም ምርቱ ገለባው መንግስታችን ከሆድ በዘለለ ለሀገር በማሰብ ከሁሉም ታርቆ የሀገሪቱን አዲስ ምዕራፍ እንዲጀምር ስል ጥሪን አስተላልፋለሁ ለህዝብ የተጣላ መንግስት እድሜው ያጥራል፡፡ 

No comments:

Post a Comment

wanted officials