Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Friday, May 22, 2015

አረና ቅስቀሣውን አቋረጠ፤ በአባሎቹ ላይ ጥቃት መፈፀሙን አስታወቀ

አረና ቅስቀሣውን አቋረጠ፤ በአባሎቹ ላይ ጥቃት መፈፀሙን አስታወቀ

ተቃዋሚው አረና ትግራይ “በአባሎቼ ላይ ተፈፅሟል” ባለው ድብደባና ለምርጫ ቅስቀሣ ሥራ በተከራያት መለስተኛ አውቶቡስ ላይ በደረሰው ጉዳት ምክንያት በመላው የትግራይ ክልል የጀመረውን የምረጡኝ ቅስቀሣ ዛሬ ማቋረጡን ይፋ አድርጓል።
አቶ ሄድሮም ኃይለሥላሴ
አቶ ሄድሮም ኃይለሥላሴ


አረና ቅስቀሣ ሲያካሂድባት የነበረች፣ ጉዳት የደረሰባት ሚኒባስአረና ቅስቀሣ ሲያካሂድባት የነበረች፣ ጉዳት የደረሰባት ሚኒባስ
አረና ቅስቀሣውን አቋረጠ፤ በአባሎቹ ላይ ጥቃት መፈፀሙን አስታወቀ
ተቃዋሚው አረና ትግራይ “በአባሎቼ ላይ ተፈፅሟል” ባለው ድብደባና ለምርጫ ቅስቀሣ ሥራ በተከራያት መለስተኛ አውቶቡስ ላይ በደረሰው ጉዳት ምክንያት በመላው የትግራይ ክልል የጀመረውን የምረጡኝ ቅስቀሣ ዛሬ ማቋረጡን ይፋ አድርጓል።
ዘጋቢያችን ግርማይ ገብሩ የተሽከርካሪዋ የኋላ መስትዋትና መብራት መሰባበሩን በሥፍራው በአካል ተገኝቶ ተመልክቷል።
ድብደባ ተፈፀመብን ከሚሉ ሰዎች መካከል ደግሞ ከአፅቢ ከተማ የመጡት አቶ ሄድሮም ኃይለሥላሴ እራሣቸው ላይ በመፈንከታቸው መቀሌ ውስጥ ሕክምና ማግኘታቸው ተገልጿል፡፡
አረና “የህወሓት ካድሬዎች ያደራጇቸው ወጣቶች አድርሰውታል” ያለውን ጥቃት አስመልክቶ የክልሉ የፀጥታና የአስተዳደር ኃላፊ አቶ ሓዱሽ ዘነበ ተጠይቀው “ተፈጽሟል የተባለውን ጥቃት ለማጣራት መርማሪዎቻችንን ወደ አካባቢው ልከናል፤” ብለዋል፡፡

No comments:

Post a Comment

wanted officials