Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, May 21, 2015

እነአብርሃ ፣ ሀብታሙ፣ የሺዋስ፣ ዳንኤል፣ …ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጣቸው

እነአብርሃ ፣ ሀብታሙ፣ የሺዋስ፣ ዳንኤል፣ …ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጣቸው
-------- 

በሽብርተኝነት ወንጀል ተጠርጥረው በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ 19ኛ ወንጀል ችሎት ጉዳያቸው እየታየ፣ እና በእነዘላላም ወርቅአፈራሁ የክስ መዝገብ ተከስሰው የሚገኙት እነሀብታሙ አያሌው፣ አብርሃ ደስታ፣ የሺዋስ አሰፋ፣ ዳንኤል ሺበሺ፣ ባህሩ ታዬ …የአቃቤ ሕግ ምስክሮችን ለመስማት ለሰኔ 1፣ 2 እና 3 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ዛሬ በችሎት ጸሀፊ በኩል እንደተሰጣቸው ጠበቃቸው አቶ ተማም አባቡልጉ ገልጸዋል፡፡
ተከሳሾቹ ወደፍርድ ቤት ቢመጡም የችሎት ጸሐፊው ‹‹ተጠርጣሪዎቹ በታሰሩበት ቦታ ከ20 ቀናት በፊት ቀኑ መቀየሩ ተናግሯቸው ነበር፡፡ እርሶንም ማግኘት ስላልቻልን ነው ቀኑን ያልነገርኖት›› እንዳሏቸው የጠቆሙት ጠበቃ ተማም በዛሬው ዕለት ችሎት ስላልተሰየመ ደንበኞቻቸው ተመልሰው ወደቂሊንጦ እንደሚያመሩ ተናግረዋል፡፡
ተከሳሾቹ፣ ከዚህ ቀደም በነበራቸው የፍርድ ቤት ውሎ ለዛሬ ተቀጥረው የነበሩት የአቃቤ ህግ ምስክሮችን በተከታታይ ቀናት ለመስማት መሆኑ ይታወሳል፡፡
Like · Comment · 

No comments:

Post a Comment

wanted officials