የቀድሞዋ የጎንደሬዎች ከተማ ሁመራ አሁን ደግሞ የጎንደሬዎች መቀበሪያዋ የጅምላ መጨፍጨፊያዋ ሁመራ በየቀኑ የወገን የድረሱልን የሰቆቃ ድምፅ ይሰማል ሁኖም ግን ሰሚ ጀሮን አላገኘም ።
ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ በሰሜን ጎንደር ምዕራባዊ ክፍል ከአማረኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያዊ የፀዳ ክልል ለመፍጠር ከ40 ዓመታት በላይ የሰራበት ቢሆን እንዳሁኑ ለይቶለት አያውቅም ቀደም ሲል በወልቃይት በጠገዴ በትግል በበረሃ እያሉ ጀምረው ነዋሪዎችን ሌሊት ሌሊት ከቤታቸው እያፈኑ የደረሱበት ሳይታወቅ የቀሩ አያሌ ወገኖች ነበሩ ።አሁን ደግሞ
በሁመራ አከባቢ ህወሀት ኢትዮጵያውያን እየረሸነ እንደሆነ የሚያጋልጥ.  መረጃወረን የሰጠው አብሮ የነበረ ወጣት ሕይወቱ በተዓምር የተረፈ የአይን ምስክር ነው ።። በሶስት ጥይቶች ተመትቶ በተአምር አምልጦ ወደ ኤርትራ የገባው አንድ ወጣት እንደገለጸው የህወሀት ሰራዊት ከመተማና ከሌሎች የጎንደር አከባቢዎች ተቃዋሚ የሚላቸውን እያፈነ ወደ ሁመራ በመውሰድ በውድቅት ሌሊት በመረሸን ላይ ነው። እስከአሁን ከአንድ መቶ በላይ ኢትዮጵያውያን ሳይረሸኑ አይቀርም።
_መተማ ዛሬ በውጥረት ውላለች። የ300አባወራዎችን ቤቶች ለማፍረስ የመጣው የመንግስት ሃይል ከነዋሪው ጋር ተጋጭቶ እስከአሁን ሁለት ሰዎች ተገድለዋል። ውጥረቱ ቀጥሏል።

_ጎንደር ሸዲ የሚገኘው የአምባሰል የጥጥ መጋዘን በደፈጣ ተዋጊ ሃይሎች ጥቃት ወድሟል። ከ600 ሺህ ኩንታል በላይ ጥጥ በእሳት ጋይቷል። አምባሰል የኢፈርት(የትግራይ መልሶ ማቋቋም ድርጅት) ንብረት ነው።
_በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ ያለው ምሬትና አለመተማመን ተባብሷል። በማዕከላዊ እዝ ሰሞኑን በተረገ ግምገማ ከአንድ ክፍለ ጦር 1ሺህ ወታደሮች ጠፍተዋል። አንድ ብርጌድ ጦር ማለት ነው………