Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Sunday, May 31, 2015

የአሜሪካ መንግስት ምርጫውን አሽሟጠጠው



የአሜሪካ መንግስት ምርጫውን አሽሟጠጠው

ወያኔን በጓንትነት የሚተቀመው የአሜሪካ መንግስት በተቃዋሚ የለውጥ ሃይሎች ላይ በሲቭል ሶሳይቲ በነጻ ሚዲያዎች እና በነጻነት ድምጾች ላይ የሚደረገው ወከባ እንደሚያሳስበው በመግለጽ የአሜሪካ መንግስት ዲፕሎማቶች ምርጫውን እንዳይታዘቡ መከልከሉንና መደረጉን በለሆሳስ አንስቶ ከአፍሪካ ሕብረት ታዛቢዎች ያገኘውን መረጃ ዋቢ በማድረግ የተቃአሚ ሃይሎች ታዛቢዎች በምርጫው ላይ እንዳይታዘቡ መደረጉ እንዳሳዘነው በመግለጽ በምርጫው ወቅት የነበረው የአፍሪካ ሕብረት ታዛብ ቡድን እንኳን የወከባዎች ተጋሪ እንደነበር ተናግሯል መግለጫው::

ለፍትሃዊ እና ነጻ ምርጫ አስፈላጊ የሆኑ ነጻ እና ለቅስቀሳ የሚሆን የመረጃ ማሰራጫ ሚዲያ የዲሞክራሲ እና የሰብአዊ መብቶች ሲቭክ ማህበራት እንዲሁም የተላያዩ አለም አቀፍ እና ሃገር አቀፍ ሕብረተሰቦች በታዛቢነት ባልተወከሉበት ምርጫ ማካሄድ አያስኬድም ሲል መግለጫው አሽሟጧል::ጋዜጠኞችን በማሰር እና በማሳደድ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን ገደብ በመስጠት የፖለቲካ ድርጅቶች ውስጥ ጣልቃ በመግባት የፖለቲካ ምህዳሮችን በማጥበብ ምርጫ ማካሄድ አይሞከርም ሲል መግለጫው ተናግሯል::



የአሜሪካ መንግስት ከኢትዮጵያ እና ከሕዝቧጋር ጠንካራ ግንኙነት አለው ያለው መግለጫው ዲሞክራቲክ ተቋማት ዕንዲጠናከሩ የፕሬስ ነጻነተ እንዲያብብ በሃገሪቱ የታፈነው የፖለቲካ ምህዳር ሁሉ ክፍት እንዲሆኑ ኢትዮጵያ የፈረመችውን የአለም አቀፍ ሰባዊ መብቶች ድንጋጌ ግዴታዎች እንድታከብር አብረን እንሰራለን ብሏል::

No comments:

Post a Comment

wanted officials