Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Wednesday, May 6, 2015

Semayawi (Blue) party chairman, Eng Yilkal Getnet, met with US State Department officials

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ከአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ኃላፊዎች ጋር ተወያዩ
የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ትናንት ሚያዝያ 27/2007 ዓ.ም ከአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ኃላፊዎች ጋር መወያየታቸውን የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡ ኢ/ር ይልቃል ጌትነት በአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት የዴሞክራሲ፣ ሰብአዊ መብትና ሰራተኞች ምክትል ዋና ፀኃፊ የሆኑት ሚስተር ስቲቭ ፌልድስቴይን ጨምሮ ሌሎችንም ኃላፊዎች አግኝተው ስለ ኢትዮጵያና ስለ ቀጠናው ሰፋ ያለ ውይይት አድርገዋል፡፡
ኢ/ር ይልቃል ከስቴት ዲፓርትመንት ኃላፊዎቹ ጋር በነበራቸው ቆይታ ስለ መጭው ምርጫ፣ ሰብአዊ መብት አያያዝ፣ የእምነት እና ሀሳብን በነፃነት መግለጽ መብት፣ ሲቪክ ማህበረሰብ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ በፀረ ሽብር ህጉና በደህንነት ስም እየተፈፀሙ ያሉ ችግሮች ላይ ተነጋግረዋል፡፡ ሚስተር ፌልድስቴይን ስለ ሰማያዊ ፓርቲ እንቅስቃሴዎች ዝርዝር ጥያቄዎችን ያነሱ ሲሆን ኢ/ር ይልቃልም በዝርዝር ማስረዳታቸው ታውቋል፡፡ በቅርቡ ምክትል የውጭ ጉዳይ ኃላፊዋ ውይንዲ ሸርማን ንግግር ላይም መወያየታቸው ታውቋል፡፡
Semayawi (Blue) party chairman, Eng Yilkal Getnet, met with US State Department officials on Tuesday May 5, 2015. In his meeting with Mr. Steve Feldstein, Deputy Assistant Secretary for Democracy, Human Rights and Labor and his staff, they discussed wide ranging topics pertaining Ethiopia and the region. The topics included among others, upcoming election, human rights, religious freedom, freedom of expression, civil societies, terrorism and security in Ethiopia and the horn of Africa. Mr. Feldstein raised several detailed questions regarding Semayawi party for which Mr. Getnet provided responses. The discussion also included the recent misstatement by under secretary Wendy R. Sherman. Details of the extended meeting will be released soon.

No comments:

Post a Comment

wanted officials