Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Friday, May 15, 2015

የዓረና_መድረክ የቅስቀሳ በራሪ ወረቀቶች በውቅሮ ተዘረፈ




አምዶም ገብረሥላሴ እንደዘገበው

የዓረና_መድረክ ኣማራጭ ፖሊሲዎች የታተመበት የውቅሮ ክልተ ኣውላዕሎ, ኣፅቢ ወንበርታ, ሓወዜን, ሳዕሲዕ ፃዕዳ እምባ ምርጫ ክልሎች ለህዝብ የሚታደል ከ12 ሺ በራሪ ወረቀቶች ባልታወቁ ሰዎች የኣቶ ቴድሮስ ሞገስ የኪራይ ቤት ቁልፍ በመስበር በጠራራ ፀሃይ ሊዘርፉት ችለዋል::

ዘረፋው የተፈፀመው በ04/ 09/ 2007 ዓ/ም ከቀኑ 9: 30 ሰዓት ሲሆን ኣቶ ቴድሮስ ከቤቱ ሲወጣ ወድያውኑ ነው:: የኣቶ ቴድሮስ የፓርቲ ኣባልነት መታወቅያ ሳይቀርና የተለያዩ የመድረክ ሰነዶችም ተዘርፈዋል::

የከተማዋ ካድሩዎች ለኣካራዩ ኣቶ ቴድሮስን ከቤቱ እንድያስወጣው በተደጋጋሚ ግዜ ከፍተኛ ማስፈራርያ ዛቻዎች ሲደርሱባቸው ነበር::
የከተማው ፖሊስ ስለ ወንጀሉ ኣብዮቱታ በቀረበበት ወቅት ጉዳዩ ለመመዝገብና ለማጣራት ከፍተኛ ዳተኝነት በማሳየት ጉዳዩ ተድበስብሶ እንዲቀር ያለው ፍላጎት ኣመላክተዋል::
ዝርፍያው የፖሊስ ወይም ድህንነት እጅ እንዳለው የሚያመላክቱ ነገሮች ለፖሊስ ኣሳውቀናል::

ጎበዝ ህወሓት የመድረክ በራሪ ወረቀት መዝረፍ ያልተወች የምርጫ ካርድ ትተዋለች ብላቹ ትጠብቃላቹ? ለነገሩ መስረቅ የለመደ ኣምባሻ ይልሳል ነው የሚባለው::
በተያያዘ ዜና በውቅሮ ክልተ ኣውላዕሎ ምርጫ ክልል የክልል ምክር ቤት እጩ ተወዳዳሪ የሆነው ኣቶ ሃይለኪሮስ ታፈረ በኣይናለም ቀበሌ ዓዲ ወረማ በተባለ የነበረ ገለባ በእሳት እንዲያያዝ በመደረጉ ሙሉ በሙሉ እንደወደመና ገለባው የተቀመጠበት ቤቶችም ወደ ኣመድ እንደተቀየሩ ታውቀዋል:: የእሳት መያያዝ ወንጀሉ በህወሓት ኣመራሮች የታዘዘና የተቀነባበረ ሴራ መሆኑ ሳይታለም የተፈታ ነው::

ህወሓት በዓረና_መድረክ ፓርቲና ኣባላቱ እያደረሰች ያለው ዓፈናዎች ለማመን የሚዳግቱ ናቸው::

No comments:

Post a Comment

wanted officials