Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Monday, May 18, 2015

የርዮት አለሙን አባት፣ (በቀድሞ ወረዳ አራት የመድረክ ተወዳዳሪ የሆኑትን)ጠበቃ አቶ አለሙን እንምረጥ !!!






የጀግና ልጅ አባት፣ እርሳቸውም የፍትህ አርበኛ የሆኑ ተወዳዳሪ - ግርማ ካሳ

የሚቀጥለው ሳምንት ምርጫ ነው። ከምርጫው የሚጠበቅ ለዉጥ ባይኖርም መድረክ እና ሰማያዊ( የአንድነት ሰዎች በብዛት በምርጫው እንቅስቃሴ ለማድረግ ስለገቡ) በጠበበው የፖለቲካ ምህዳር ዉስጥም ሆነ ሕዝቡን ለማንቀሳቀስ ጥረት እያደረጉ ነው። በተለይም መድረክ በኦሮሚያና በትግራይ ብዙ ድጋፍ እያገኘ እንደሆነ የሚያሳዩ ምልክቶች አሉ።


መድረክን እና ሰማያዊ ወክለው ለፓርላማ ከሚወዳደሩ በርካታ ኢትዮጵያዊያን መካከል እኝህ አባት ይገኙበታል። በሞያቸው ጠበቃ ናቸው። የመልካም ሴት ባላቤትና የተባረኩ ልጆች አባት ናቸው። ከእኝህ አባት ሴት ልጆች መካከል አንዷ አስተማሪ ሆና ነበር። ከደሞዟ ብዙ ችግር ያለባቸውን ተማሪዎች ትረዳና ትደግፍ ነበር። እንደ ዜጋ ሕግ መንግስት በሚፈቅደው መሰረት ጻፈች፣ አስተያየቷን ሰጠች።

እነርሱ መስማትና ማንበብ ከሚፈለጉት ዉጭ እንዲጻፍና እንዲነገር የማይፈልጉት ገዢዎች፣ የአስተሳሰብ ድሆች በመሆናቸው፣ ብእሯን መመከት አልቻሉም። ወደ ጡንቻ ሄዱ። አሰሯት። በዉሸት ክስ ሽብርተኛ ናት ብለው ከሰሷት። ጠበቃ አባቷ ተከራከሩ። ሆኖም ፍርድ ቤቶች የፍትህ አካላት ሳይሆን የሕወሃት ፖሊት ቢሮ ጉዳይ አስፈጻሚዎች በመሆናቸው፣ ፍትህ ሊገኝ አልቻለም። ይች ወጣት ለአመታት በቃሊቲ ትሰቃያለች። ይች ወጣት ርዮት አለሙ ትባላለች። በዘመናችን ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው ብርቅዬና ጀግና ኢትዮጵያውያን መካከል አንዷ !!!!

ጠበቃ አባቷ፣ ምን ያህል የሕግ ስርዓት እንደሌለ በመረዳታቸው፣ ፍትህ ከፍርድ ቤት እንደማይገኝ በማወቃቸው ለዚህ ደግሞ በዋናነት ምክንያቱ የተበላሻዉና የበሰበሰው የፖለትካ ስርዓቱ በመሆኑ፣ ይሄንን ስርዓት ለመለወጥ በቀድሞ ወረዳ አራት የመድረክ ተወዳዳሪ ሆነው በድጋሚ ቀርበዋል። እኝህ አባት ጠበቃ አለሙ ጎቤቦ ይባላሉ።

ትግል የሁሉንም ተሳትፎ ይጠይቃል። ጠበቃ አለሙ በጥብቅና ሞያቸው ቀጥለው፣ ፍትህ ቢጓደልም “ ምን አገባኝ” ብለው መቀመጥ ይችሉ ነበር። ሆኖም ከራስ አልፎ ለሌላ መቆም ትልቅነት ስለሆነ፣ እኝህን አባትም ትልቅ አባት ስለሆኑ፣ ዝምታን አልመረጡም። ከዚህ በፊት እንዳደረጉት ሁሉ በፖለቲካዉ ትግል አምባገነንነትን ለመታገል ተነሱ።

የርዮት አለሙን አባት፣ የኛም የነጻነት ናፋቂዎች ሁሉ አባት የሆኑትን፣ አቶ አለሙን እንምረጥ !!!!! አገዛዙ ከአምስት አመታት በፊት እንዳደረጉት ድምጽ እንዳይሰርቁም፣ ድምጹ እስኪቆጠር ድረስ፣ ሕዝቡ በየምርጫ ጣቢያ ቁጭ ብሎ በመጠበቅ ራሱ ማስቆጠር አለበት። 3፣ 4 አጋዚ፣ ፌዴራልና ካድሬ ፣ ሺሆችን አስፈራርተው የሕዝብ ድምጽ እንዲሰርቁ ሊፈቅድላቸው አይገባም።

No comments:

Post a Comment

wanted officials