Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Sunday, September 13, 2015

አርቲስት ሰብለ ተፈራ በመኪና አደጋ ሕይወቷ አለፈ።ባለቤቷ ታስሮ ይገኛል









አርቲስት ሰብለ ተፈራ በበርካታ ፊልሞች እና ድራማዎች ላይ ተውናለች በተለይም በኤፍቢሲ ሲተላለፍ በነበረው <<ትናናሽ ፀሀዬች>> በተሰኘው የሬድዮ ድራማ የእማማ ጨቤ የተሰኙ ገፅ ባህሪ በመወከል ተጫውታለች።

ቅዳሜ ምሽት በኢቢሲ እየተላለፈ በሚገኘው ቤቶች ድራማ ላይም ትርፌ በሚለውን ገፀባህሪዋ በርካታ ተከታታዮችን አፍርታለች


መስከረም 1/2008 እንደደረሰን መረጃ ከሆነ ሳሪስ አካባቢ በደረሰ የመኪና አደጋ የአርቲስቷ ሂወት አልፏል።
ባለቤቷ ሞገስ ተስፋዬ አደጋው ከተፈጸመ በኋላ በ እስር ላይ ይገኛል  :: ፖሊስም ስለአደጋው አፈጣጠር ምርመራ እያደገበት ይገኛል::  ነገ ሰኞ በመንበረ ጸባኦት ቅድሥት ሥላሴ ካቴድራል ከቀኑ በ9፡00 ሰዓት በሚፈጸመው የባለቤቱ የቀብር ሥነስርዓት ላይ ሞገስ   በፖሊስ ታስሮ እንደሚገኝ የጠቆሙት  ምንጮች ለፖሊስ አደጋው የተፈጸመ ሙዚቃ ለመቀየር ጎንበስ ሲል እንደሆነ ተናግሯል:: አርቲስት ሰብለ ተፈራ እና ባለቤቷ ሞገስ ተስፋዬ ይህ የመኪና አደጋ ከመፈጸሙ ከቀናት በፊት በአቡዳቢ እና በዱባይ ለእረፍት (ቫኬሽን) ወጥተው መልካም ጊዜ ማሳለፋቸውን ባለቤቷ በፌስቡክ ገጹ ለጥፎ ነበር::

ለወዳጅ ዘመዶቿ እንዲሁም ለአድናቂዎቿ መፅናናትን እንመኛለን።










No comments:

Post a Comment

wanted officials