Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Wednesday, September 2, 2015

ሰበር ዜና በዲሲ ትላልቅ ቤተክርስቲያን ላይ ወያኔ አዲስ ዘመቻ ጀመረ










ሰኞ ነሐሴ 26 ቀን 2007 ዓ.ም.

ለዚህ ማስረጃ የሚሆኑ ሰሞኑን በዋሽንግተን ዲሲ እየታዩ የሚገኙት ሁለት አንጋፋ ቤተክርስቲያኖች ላይ የተከሰጠውን ዘገባዎች ይዘን ቀርበናል። በቅድሚያ ይህን ሪፖርት እንድናጠናቅር የተባበሩን ሁሉ በቅድሚያ እናመሰግናለን። የርዕሰ አድባራት ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በዋሽንግተን ዲሲ የምትገኘው የርዕሰ አድባራት ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እሁድ ነሐሴ 24 ቀን 2007 ዓ.ም. (August 30, 2015) የተክለሃይማኖት ታቦት በሚወጣበት ዕለት ከፍ ያለ ግርግርና ረብሻ እንደነበር ከስፍራው የደረሰን ዜና ያመለክታል። የተክለሃይማኖትን በዓል ለማክበር ከየአድባራቱ የተሰበሰቡ ምእመናን ባሉበት የሰንበት ት/ቤት ወጣት መዘምራን አንድ መዝሙር ከዘመሩ በኋላ፣ ታቦት ከመውጣቱ በፊት መግለጫ አለንና እናነባለን የሚል ጥያቄ ሲያነሱ የደብሩ አስተዳዳሪ የሆኑት ሊቀ ማዕምራን ዶ/ር አማረ ካሳዬ የቤተክርስቲያኑን አሰራር የጣሰ ጥያቄ ስለነበር ማንበብ አትችሉም አሏቸው። ለምን ይህ እንደሆነ የጠየቅናቸው ግለሰቦች እንደሚሉት ሊቀ ማዕምራን ዶ/ር አማረ ትክክል ናቸው ምክንያቱም የታቦተ ሕጉ ሳይፈፀምና ፈቃድ ባልተጠየቀበት ሁኔታ ማንኛውንም ማታወቂያ ማንበብ በቤተክርስቲያን የማያስፈልግ ኹከት ያስከትላል የሚል ነው። ነገር ግን ከካህናቱ መካከል ዘማርያኑን ነገር ጎስጉሰው ሴራውን ያዘጋጁ ስለነበሩ፣ የቀሲስ አማረን ሃሳብ ውድቅ አድገው፣ ያንብቡ በማለታቸው መዘምራኑ መግለጫቸውን አንብበዋል። ሌሎች በዙሪያው የነበሩ ሰዎችን አነጋግረን የተረዳነው ለመበጥበጥ ሙከራ ሲደረግ ጉዳዩን ያቀዱና ወጣቶቹን ያሰማሩ ሰዎች ፈንጠር ብለው ተቀምጠው እየሳቁ ያዩ ነበር። ከነዚህም ውስጥ እነ ቄስ ተስፋዬ መቆያና ዶ/ር አክሊሉ ሐብቴ ይገኙበታል። ሌሎች ያነጋገርናቸው ጠለቅ ያለቅ ግንዛቤና ተሞክሮ አላቸው የሚባሉ ሰዎች እንደሚሉት ወያኔ እንግሊዝ አገር እንዳደረገው ዋሽንግተን ዲሲ ላይም ለምድገም ይመስላል የሚሉም አሉ። እንዴት ነው ከለንደን ጋር የሚመሳሰለው ብለን ስንጠይቃቸው እንዲህ አሉን። ለንደን ደብረጽዮን የሆነው የሰባካ ጉባኤ አባለት ( 4 ካህናት፣ 1 ከሰንበት ት/ቤት እና 4 ከምዕመናን) የተውጣጡ ነበር። ከነዚህ ዉስጥ 4 የምእመናን ተወካዮች በጣም ስለተሰላቹና የወያኔ እቅዱ ስላገባቸው ጥለው ወጡ። በዚህን ወቅት 4 ካህናት፣ 1 ከሰንበት ት/ቤት አብላጫ ድምጽ ይዞ ቤተክርስቲያኗን ከሁለት ዓመታት በላይ ውዝግብ አስነስቶ አሁን ወደ መጨረሻው የሆነው ታማኝ የሆኑና የወያኔ ተንኮል የገባቸው ምዕመናን አዲስ ኮሚቴ በመመረጡ ነው። አባ ግርማ አሁን ለንደንን ለቀው ደብረዘየት አካባቢ ቤተ አስርተው ሊኖሩ ሄደዋልም የሚል ወሬም በማህበራዊ ድረ ገጾች ተነቧል። ታዲያ እንዴት እነዚህ መዘምራን ሁሉም ጉዳዩን አምነውበት ነውን? ብለን የጠየቅናቸው ምንጮቻችን፣ ወጣቶቹ ይህን የተወሳሰበ ተንኮል ከጥቂቶቹ በስተቀር አያቁም። ነገር ግን ስርዓተ አልበኛነት ማሳየታቸው እጅግ የሚያሳፍር ጉዳይ ነው ይላሉ። ቀጥለውም ለእግዚአብሔር አግልግሎት የተሰጠውን የድምፅ ማጉሊያ አጋጣሚ በመጠቀም የጉዳዩ ኹከት ፈጣሪ መሆናቸው አሳፋሪ ጉዳይ ነው ብለዋል። በዲያስፖራ የሚከሰተውን የወያኔን የቤተክርስቲያን የማጥፋት ዘመቻ በቅርብ የሚከታተሉት እንደሚሉት ደግሞ በዋሽንግተን ዲሲና ካሊፎርኒያ አሜሪካ ግዛዛት ሊቀ ጳጳስ የሆኑት አባ ፋኑኤል የዘመቻው ዋና አቀንቃኝ እንደሆኑ ይናገራሉ። አባ ፋኑኤል የወያኔን መመሪያ ተግባራዊ እንዲሆን በተሰጣቸው ትዛዝ መሰረት ህዝበ ክርስቲያኑን የሚከፋፈልበትን ዘዴ የሚረዷቸው የእግር ወታደሮች አሰባስበዋል። የሆኑት በየቦታው (ዳላስ፣ ለንደን፣ሚኖሶታ፣ ናሽቪል፣ ቦስተን፣ ወ.ዘ.ተ.) እንዳየነው ወጣት መዘምራን ቀደም ብለው ያዘጋጁት የአቋም መግለጫ ማንበብ አለብን ማለታቸው ነው። ታቦተ ሕጉ ሳይወጣ በአውደ ምህረት ላይ ቆመው ሁከት ለማስነሳት የሞከሩት ከጩኽትና ግርግር በኋላ ሊቀ ማዕምራን አማረ ፈቅደውላቸው አንብበዋል። ወጣቶቹ ከጠየቋቸው አንዳንድ ጥያቄዎች ውስጥ የቄስ ኃይሉ ከባለአደራ ቦርድ ለምን ተባረሩ፣ ይመለሱ የሚል ይገኝበታል። በመሰረቱ ቄስ ኃይሉ ከባለአደራ ቦርድ መወገዳቸውንና አለመወገዳቸውን ለማጣራት ባደረግነው ሙከራ፣ ቄስ ኃይሉ እንዳልተባረሩ ነው። ይህን ጉዳይ ቄስ ኃይሉ ምናልባት ከጀርባ ሆነው ወጣቶችን የሚገፉ እነ መምህር ተስፋዬ መቆያ ናቸው የሚል አስተያየት ይሰጣሉ ። ስል መምህር ተስፋዬ መቆያ ሌላ ዘገባ እናቀርባለን። ወጣቶቹ ትርምስ በመፍጠር ቤተክርስቲያኗን በለንደን ደብረጽዮን ማርያም ቤተክርስቲያን የተከሰተውን ችግር ለመፍጠር የታሰበ ይመሰላል የሚሉም አሉ። ባለፈው ሳምንት ስለ አቶ አዲሱ አበበ በዋሽንግተን ዲሲ ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ጋር የገባውን ውጣውረድ ዘግበን ነበር። አቶ አዲሱ የቤተክርስቲያኑን ባለአደራ ቦርድ ለማሳጣትን ብዙ ዘመቻ የሚያደርገው አንዳድ ለሆዳቸው ያደሩ ደፍተራዎችን በመጠቀም ነው። የነዚህን ሆድ አደር ደፍተራዎች ዝርዝር ጉዳይ በሌላ ዘገባ እንመለስበታለን። ደብረ ገነት መድኃኔ ዓለም የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በተመሳሳይ መልኩ በሜሪላንድ ደብረ ገነት መድኃኔ ዓለም የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በመምህር ዘበነ ለማ አማካይነት ለረዥም ዓመታት ውስጥ ውስጡን ሲበስል የነበረው ቤተክርስቲያኑን በቀጥታ ወያኔ ቁጥጥር ሥር የማስገባት ሂደት የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሱን ለዝግጅት ክፍላችን የደረሰው መረጃ ያመለክታል። በዚህም መሠረት ባለፈው አስራ አምስት ቀናት በፊት መምህር ዘበነ ለምዕመናን ባስተላለፈው ትዕዛዝ መሠረት እያንዳንዱ የቤተክርስቲያኑ አባል በሚመደብለት ነፍስ አባት ካህን ስር አንዲመዘገብና ይህንን የሚቃወም ማንኛውም ካህን ለቆ መሄድ አንዲሚችል አስጠንቅቋል። እያንዳንዱ ምዕመን በራሱ ፍቃድና ውሳኔ የፈለገውን ካህን ከፈለገበት ደብር የመያዝ መብቱን የጣሰና ከተዋህዶ ቤተክርስቲያን ህጋት ውጭ የሆነው የመምህር ዘበነ መመሪያ ብዙ የዲሲን አካባቢ የኦርቶዶስ ቤተክርስቲያን ምዕመናን በማነጋር ላይ የሚገኝ ጉዳይ ሆኗል። ከ30 ዓመታት በላይ በቤተክርሲያኑ አባል የሆኑ አንዳንድ ምዕመናን እንደሚናገሩት ከሆነ የመምህር ዘበነ ዕቅድ ቁጥራቸው ከ200 የማይበልጠውን የቤተክርስቲያኑን አባላት ከ10 እስከ 12 ቁጥር ባላቸው ካህናት ሥር በመመደብ፣ ምዕመናኑ በሚመደቡላችው ካህናት የሚተላለፉላቸውን መመሪያዎች መቀበልና በምዕመናን ስብሰባ ላይ ለውሳኔ የሚቀርቡ ሃሳቦችን ከነፍስ አባታቸው በተነገራቸው መሠረት ድምጽ እንዲሰጡ ለማስደረግ መሆኑና እንዲሁም ምዕመናኑ መንፈሳዊና ዕለታዊ ኑሮ ላይ ቁጥጥር ለማድረግ ነው የሚሉት ይገኙበታል። ይህንንም በአገራችን ላይ በወያኔ አስገዳጅነት እያንዳንዱን ዜጋ “አንድ ለአምስት መጠርነፍ ከተባለው አሰራር ጋር የተያያዘ የእዝ ሰንሰለቱን ጠብቆ ሊካሄድ ዝግጅቱ መጠናቀቁን ተደርሶበታል። ከነዚህም በስውር እየተሰራባቸው ካለው አብይ ጉዳዮች አንዱ በዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ በወያኔ የተሾሙትን አቡነ ፋኑኤል (አባ መላኩ ጌታነህ) በደብረገነት መድኃኔ ዓለም ቤተክርስቲያን ተቀባይነትና እውቅና እንዲያገኙ ለማድረግና ቀጥሎም ቤተክርስቲያኑን በአቡነ ማቲያስ በሚመራው የኢትዮጵያው ሲኖዶስ ስር ለማስገባት ነው። እስከ አሁን ድረስ ቤተክርስቲያኗ በውጭ ከሚገኘው ሲኖዶስም ሆነ ከአገር ቤቱ ሲኖዶስ ሳትወግን በራስ ገዝ (independent ገለልተኛነት) የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ እምነትና ሥርዓቱን ብቻ እየተከተለች ከ30 ዓመታት በላይ የዘለቀች መሆኑ ይታወቃል። ሆኖም በደረሰን መረጃ መሠረት መምህር ዘበነ ኢትዮጵያ እየተመላለሰ ለማስተማርም ሆነ ለግል ጉዳይ የሚያደርገውን ተደጋጋሚ ጉዞ ከአቡነ ፋኑኤል የመሸኛ ደብዳቤ ካልያዘ በስተቀር እንደማይፈቅድለት በማስጠንቀቂያ መልክ በተነገረው መሠረት ቤተክርስቲያኗን ወደ አገር ቤት ሲኖዶስ ለማስገባት ያቀደው ዘዴ አንደሆነ ይናገራሉ። የቤተክርስቲያኗን ታሪክና ከአቡነ ማትያስ ጋር የነበረውን ግንኙነት ዘርዝረው እንዲያስረዱን የጠየቅናቸው መስራች ምእመናን የሚከተለውን ነግረውናል። የደብረገነት መድኃኔ ዓለም ቤተክርስቲያን ከ20 ዓመታት በፊት አሁን ፓትርያርክ በሆኑት አቡነ ማቲያስ ከወያኔ የተሰጣቸውን የሰሜን አሜሪካ የሊቀ ጵጵስና ሹመት አመዛኙ የደብረ ገነት ቤተክርስቲያን አባላት አንደተቃወሙና በዚህም ምክንያት አቡነ ማትያስ በመቶ ሺዎች የሚገመት ገንዘብ ዘርፈው ሄደዋል። ገንዘቡን ሊወስዱ የቻሉት ወ/ሮ ሐረገወይን የምትባል የገንዝብ ያዥ በመሆኗና እርሷ ደግሞ ከአቡነ ማትያስ ጋር ጵጵስናን የማይመጥን ህገወጥ ግንኙነት ስለነበራት በሷ አማካይነት ነበር ይላሉ። በገንዘብ የተነሳ በውጭ አገር ከሚገኙ የኢ/ኦ/ተ/ ቤ/ክ ለመጀመሪያ ጊዜ ዓለማዊ ፍርድ ቤት ድረስ በመሄድ አቡነ ማትያስ ፋና ወጊ ጳጳስ ተብለው ሊጠቀሱ የሚችሉ ናቸው ይላሉ። ጉዳዩን የሚያወቁት ምንጮቻችን እንደሚሉት በገንዘብ በተነሳው የፍርድ ቤት ክርክር ከፍተኛ ገንዘብ እንዲባክን ሆኗል። በተጨማሪም “አቡነ ማትያስ ሲያጠምቁ፣ ሲባርኩና ስያቆርቡ የኖሩበትን የደብረ ገነትን ክርስቲያኞችን አውግዘው የተለዩትን ሕዝበ ክርስቲያን እንዴት ሆኖ ነው በአቡነ ማትያስ ስር የምንሆነው? ይሄ እጅግ የሚያሳፍርና የሃይማኖትንም ሕግንም የጣሰ ነው በማለት በቁጭት ይናገራሉ። ከአምስት ዓመት በፊት መምህር ዘበነ የቤተክርስቲያኑ አለቃ አንዲሆን ከፍተኛ እርብርቦሽ ባደረጉና ይህ ሹመት ለመምህምር ዘበነ ለማ “አይገባውም፣ይብሰል፣ ምራቁን ይዋጥ ባሉ ምዕመናን መካካል ተፈጥሮ ከነበረው ውዝግብ በስተቀር ለረዥም ዓመታት ቤተ ክርስቲያኑ መተዳደሪያ ደንቡን ጠብቆ የአስተዳደር ቦርድ አባላቱን በመምረጥ በሰላምና በፍቅር እንደ ቤተሰብ ሆኖ የቆየ አንጋፋ ደብር እንደሆነ እነዚህ ምዕመናን ይናገራሉ። ሆኖም ከአምስት ዓመት በፊት በመምህር ዘበነ ምክንያት በቤተክርስቲያኑ ውስጥ ተፈጥሮ የነበረው ንትርክና ጭቅጭቅ እንዲሁም አባላት በወሰዱት አቋም ምክንያት ከረዥም ዓመታት ወዳጆቻቸው ጋር አጣልቷቸው የነበረው የአንድ ግለሰብ ጉዳይ አሁንም መልኩን ቀይሮ ተመልሶ መምጣቱ እንዳሳዘናቸው ገለጸውልናል። ከዚህ ጋር ተያይዞ አንዳንድ ለወያኔ ወሬ የሚያመላልሱ ግለሰቦች ከምዕመናኑ ጋር ተቀላቅለው ቤተክርስቲያኑን ለወያኔ ለማስገባት በመህር ዘበነ ለማ የሚሰጠውን ቤተክርስቲያኑ ኢትዮጵያ ውስጥ በሚኘው ሲኖዶስ ውስጥ ካልገባ በስተቀር ትክክለኛ ቤተክርስቲያን ተብሎ ሊጠራ አይችልም “ የሚል በማር የተለወሰ መርዝ በምዕመናን ጭንቅላት ውስጥ እንዲቀረጽ ከፍተኛ ጥረት ሲያደርጉ መቆየታቸውን ይናገራሉ። ቀጥለውም ሲያብራሩ መምህር ዘበነ ለማ በሸረበው አዲሱ እያንዳንዱ ምዕመን በነፍስ አባት ስር የማደራጀትና የመጠርነፍ ተንኮል ያሰበውን ለማሳካት ሙከራዎችን በማድረግ ላይ ይገኛል። በዚህም ጉዳይ ላይ ተጨማሪ መመሪያ ከወያኔው ንቡረ ዕድ ኤሊያስ አብርሃ ለመቀበል የእንቁጣጣሽን በዓል ከምዕመናን ጋር ካከበረ በኋላ ወደ አዲስ አበባ እንደሚበርም የደረሰን መርጃ ይጠቁማል። ይህንን በግልጽ የሚደረግ የወያኔን ሴራ በተለይም በነፍስ አባት ስም የሚካሂደውን ጥርነፋ እንዴት ምዕመናን ተቀብለው እንደሚቀጥሉ የሚታይ ይሆናል። የኢትዮጵያ ሕዝብ ይህንን ጥርነፋ ጠመንጃ ተደግኖበት፣ ሳንጃ ተወድሮበት በግዳጅ እላዩ ላይ ቢጫንበትም እዚህ የዲሞክራሲ ማዕከል በሆነችው አሜሪካ ውስጥ እየኖሩ በተወናበደና በተጣረሰ ትምህርት በነፍስ አባት ስም እራሳቸውን በፈቃዳቸው ለማስጠርነፍ የሚቀበሉ ካሉ ወያኔ ምን ያህል መሰሪ መርዙን በውጭው ዓለም መርጨት መቻሉን የሚያሳይ ይሆናል። ከዚህም በተጨማሪ የደብረ ገነት መድኃኔ ዓለም ካህናት በመምህር ዘበነ ምክንያት ከፍተኛ ጫና እየደረሰባቸው እንደሆነና ብዙዎቹ ከስራና ከደመወዝ እንዳይታገዱ ወይም እንዳይባረሩ ተሳቀው እንደሚያገለግሉ ይናገራሉ። በተለይም በቅርቡ የሊቢያን ሰማዕታት አስመልክቶ በዋሽንግተን ሞኑመንት አጠገብ በተደረገው የመታሰቢያ ሥነ ሥርዓት ላይ በውጭ ከሚገኘው በአቡነ መርቆርዮስ ከሚመራው ከዉጪው ሲኖዶስ የመጡ ጳጳስ ከመገኘታቸው ጋር በተያያዘ ለውጭው ሲኖዶስ ታማኝነታቸውንና አክብሮታቸውን የገለጹ ካህናት ከመምህር ዘበነ ትንኮሳና ጥቃት እየደረሰባቸው እንደሆነ ታውቋል። በተለይም አንዱ አንጋፋ ካህን ለረዥም ዓመታት ከክፍያ ነጻ ማገልገላቸው ሳያንሳቸው እንደ አንድ ምዕመን የአባልነት ክፍያ እየፈጸሙ ቤተክርስቲያኑን በገንዘባቸው፣በጉልበታቸውና በክህነታቸው የሚረዱ ጠንካራ ካህን ቤተክርስቲያኑን በወር $5,000 የሚያስወጣው ካህን ሊገፋቸው መፈለጉና የአስተዳደር ቦርዱ ይህንን ግፍ ለማስወገድና እኝህን ጠንካር አባት ሊታደጋቸው አለመቻሉ ብዙዎቹን ምዕመናን እንዳሳዘነ ለመረዳት ችለናል። በዚህ ጉዳይ ጋር ተያያዥነት ያላቸው የደረሱንን ሌሎች መረጃዎችን ትክክለኛነት አጣርተን መረጃዎቹን ለህዝብ ዕይታ እንደምናደርስ ከወዲሁ እናስታውቃለን።

No comments:

Post a Comment

wanted officials