Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, June 25, 2015

ሰበር ዜና - የእንግሊዝ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዛሬ ሐሙስ ሰኔ 18/2007 ዓም በአቶ አንዳርጋቸው ጉዳይ ባወጣው መግለጫ የኢህአዴግ/ወያኔን መንግስትን ማስጠንቀቁን ሮይተርስ ዘገበ።



ሰበር ዜና
የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በአቶ አንዳርጋቸው አያያዝ ዙሪያ ማስጠንቀቂያ ሰጡ
ሰኔ ፲፰ (አስራ ሰምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አቶ አንዳርጋቸው የህግ ድጋፍ በማያገኙበትና ይግባኝ ሊጠይቁ በማይችሉበት ሁኔታ በአስከፊ ሁኔታ መታሰራቸውን የእንግሊዝ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ፊሊፕ ሀሞንድ አውግዘዋል።
የአቶ አንዳርጋቸው አያያዝ እና ደህንነት እንደሚያሳስበን በተደጋጋሚ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቴዎድሮስ አድሃኖም ብንገልጽም ከቃል ያለፈ መልስ አለገኘንም፣ የምክር እና ራሳቸውን መከላከል የሚችሉበት መብትም አላገኙም ሲሉ የገለጹት ሚኒስትሩ፣ በተደጋጋሚ ለቀረበው ጥያቄ ኢትዮጵያ መልስ መንፈጓ ከፍተኛ ዋጋ በሚሰጠው የእንግሊዝና የኢትዮጵያ ግንኙነት ላይ ጥላ አደጋ ያስከትላል ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ አንዳርጋቸው በአስቸኳይ የህግ ድጋፍና ምክር እንዲያገኙ፣ በቤተሰቦቻቸውም እንዲጎበኙ መንግስት እንዲፈቅድ ለቴዎድሮስ አድሃኖም መናገራቸውንም የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ ባወጠው መግለጫ ጠቅሷል።
አቶ አንዳርጋቸው በየመን ተላልፈው ከታሰሩ ልክ አንደኛ ዓመት መሆናቸውን አስመልክቶ የተሰጠው መግለጫ በአዲስ አበባው መንግስት የተወሰደው እርምጃ ተቀባይነት እንደሌለው በግልጽ ያመላከተ ነው ተብሏል።
የውጪ ጉዳይ ቢሮው ጉዳዩን ከዲፕሎማሲያው ልውውጥ በላይ በማድረግ ለአደባባይ ማብቃቱን ዘጋርዳያን ዘግቧል።
ከእንግሊዝ መንግስት ከፍተኛ እገዛ የሚያገኘው ኢህአዴግ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ለሰጡት ማስጠንቀቂያ የሰጠው መልስ በመግለጫው አልተጠቀሰም።
ኢህአዴግ በውጭ ሃይሎች ግፊት እንደማይንበረከክ በተደጋጋሚ ሲገልጽ ቆይቷል። አቶ መለስ ዜናዊ በአንድ ወቅት የኢህአዴግን እጅ ሊጠመዝዙ የሚፈልጉ ሁሉ ገንዘባቸውን ይዘው በሊማሊሞ መሄድ ይችላሉ ብለው ነበር።

የሮይተርን ሙሉ ዘገባ ከእዚህ በታች ይመልከቱ።

LONDON
UK tells Ethiopia its treatment of opposition official imperils ties
The British government told Ethiopia on Thursday its treatment of an imprisoned opposition figure, who is also a British national, was unacceptable and that the case risked hurting ties between the two countries.
Andargachew Tsige was sentenced to death in 2009 in absentia over his involvement with an opposition political group and another trial handed him life behind bars three years later. He was arrested in Yemen in 2014 and extradited to Ethiopia.
British Foreign Secretary Philip Hammond said on Thursday he had discussed the matter with Tedros Adhanom Ghebreyesus, his Ethiopian counterpart, and delivered a stern message.
"I am deeply concerned that, a year after he was first detained, British national Andargachew Tsige remains in solitary confinement in Ethiopia without a legal process to challenge his detention," Hammond said in a statement after the call.
"I am also concerned for his welfare and disappointed that our repeated requests for regular consular access have not been granted, despite promises made."
Britain summoned Ethiopia's chargé d'affaires in August last year to seek assurances that Tsige would not be put to death.
Secretary-general of the Ginbot 7 political group, he was among 20 opposition figures and journalists charged with conspiring with rebels, plotting attacks and attempting to topple the government.
Hammond said Britain's ties with Ethiopia were at risk.
"Ethiopia's failure to grant our repeated and basic requests is not acceptable," he said. "The lack of progress risks undermining the UK’s much valued bilateral relationship with Ethiopia."
(Reporting by Andrew Osborn; Editing by Stephen Addison )
Source - Reuters

No comments:

Post a Comment

wanted officials