Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Saturday, June 20, 2015

ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ አንድ የመድረ ክአባሉ ተገድለው መገኘታቸውን አስታወቀ


መድረክ አባሉ በደቡብ ኢትዮጵያ ተገድድቦ መገደሉን ገለጸ
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ አንድነት መድረክ በደቡብ ክልል አንድ የምርጫ አስተባባሪው አርብለት ተገድለው መገኘታቸውን አስታወቀ። የተቃዋሚ ፓርቲም በምርጫ 2007 ዙሪያ የዛሬውን ጨምሮ 4 አባላቱና ደጋፊዎቹ መገደላቸውን አስታውቋል።
በዚህ ሳምንት እንደተገደሉ ተቃዋሚዎች ከገለጿቸው ሶስት ሰዎች በተጨማሪ በኦሮሚያና ደቡብ ክልል ህይወታቸው ማለፉ የተገለጸው አጠቃላይ ቁጥር ስድስት ደርሷል።
በደቡብ ክልል ሀዲያ ዞን ሶሮ ወረዳ የተገደሉት አቶ ብርሃኑ ኤረቦ በትናንትናውለት በሁለት ፖሊስ ባልደረቦች ከመኖሪያ ቤታቸው ከተወሰዱ በኋላ ተደብድበው ህይወታቸው አልፎ ወንዝ ዳር መገኘታቸውን የመድረክ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ምርጫ 2005 በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ ወደ 46ሽህ የሚጠጉ የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ሰላማዊ በሆነ መልኩ መከናወኑን የኢትዮጵያ መንግስትና ምርጫ ቦርድ ይገልጻሉ። የተቃዋሚ ፓርቲዎች ሂደቱ በወከባ እስራትና አልፎ አልፎ ግድያዎች የታዩበት ነው በሚል፤ ሂደቱንና ውጤቱን አንቀበለም በማለት መግለጫዎች አውጥተዋል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials