Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Friday, June 26, 2015

በዛሬው እለት አዲስ አበባ በሚገኘው በታላቁ አንዋር መስጅድ ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ ተደረገ!





በዛሬው እለት አዲስ አበባ በሚገኘው በታላቁ አንዋር መስጅድ ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ ተደረገ!

ትናትም ዛሬም “ኮሚቴው ነፃ ነው.. በነፃ ይሰናበት” እያሉ ፍትህን የሚጠይቁ ሙስሊሞች በአንዋር መስጊድ ደማቅ ሰላማዊ ተቃውሞ ሲያሰሙ ዋሉ:: በተያዘው የረመዳን ጾም የሕወሓት መንግስት ካንጋሮው ፍርድ ቤት እስር ቤት ባሉት የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ላይ ፍርድ ለመስጠት ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረ ቢሆንም ላልተወሰነ ጊዜ ማራዘሙ መዘገቡ ይታወሳል:: ዛሬ በአንዋር መስጊድ እና በተመረጡ የክልል ከተሞች በተደረገው በዚሁ የድምፃችን ይሰማ ተቃውሞ ሕዝቡ መፈክሩን በመያዝ በየመስጊዱ ኮሚቴውን በነጻ ከመልቀቅ የተሻለ አማራጭ የለም ሲል በአንድ ድምጽ ሲያሰማ ውሏል:: “የተከሰሰነው ነው እኛ ነን:: በነፃ ከማሰናበት ውጭ ያነሰን ብይን ያለ አማራጭ አንቀበልም” ያሉት ሕዝበ ሙስሊሙ ማህበረሰብ አባላት መንግስትን አሁንም በሰላማዊ መንገድ ፍትህ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል::

ይህንን የበከተ በዴሞክራሲናፍትሕ ላይ የሚቀልድ ነዉረኛ ስርዓት ከዚህ በኋላ ባመጽ መንገድ አሽቀንጥሮ ለመጣል የንደዚህ አይነቱ ቁርጠኛና አይበገሬ ትግል ወሳኝም ታሪካዊም ነዉ፥ሁሉም ወገን በየፊናው ድምጹን ያሰማ !




No comments:

Post a Comment

wanted officials