Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Monday, June 15, 2015

የሰላም በሮች ሲዘጉ የአመጽ በሮች ይከፈታሉ የአንድነቱ አብርሃምም የብረት ትግሉን ተቀላቅሏል

የሰላም በሮች ሲዘጉ የአመጽ በሮች ይከፈታሉ
የአንድነቱ አብርሃምም የብረት ትግሉን ተቀላቅሏል
የቀድሞው አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ከዓመት በፊት ጠቅላላ ጉባኤውን በአዲስ አበባ ሲያከናውን ከየክልሉ የመጡ ተሳታፊዎችን የማግኘትና በክለላቸው ስለሚያደርጓቸው እንቅስቃሰዎች፣ስለሚደርስባቸው እስራት፣ወከባ፣ድብደባና ስለሚፈጸሙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እንዲያካፍሉን የፍኖተ ነጻነት ጋዜጣ ባልደረቦች እንወተውታቸው ነበር፡፡
አብርሃም ልጃለም ከጎንደር አካባቢ ወደ አዲስ አበባ ለጠቅላላ ጉባኤው የራሳቸውን የትራንስፖርት ወጪ ችለው ከመጡ የክልሉ የአንድነት አመራሮች አንዱ ነው፡፡ጎንደሮች አዲስ ሲመጡ ባዶ እጃቸውን አልመጡም፡፡ገበሬውን ወላጅ አባቷን በመኖሪያ ቤቱ በጥይት ደብድበው ከገደሉት በኋላ በተኛችበት የመደብ አልጋ በተተኮሰባት ጥይት የቀኝ እጇን ለመቆረጥ የበቃችን የስምንት ዓመት ታዳጊ ወጪዋን ሸፍነው አምጥተዋት ነበር፡፡
አብርሃም ልጃለምና ጓደኞቹ በክልላቸው ስለሚፈጸም የመብት ጥሰት የሚያወሩት በቃል አይደለም፡፡ስለሚያወሩት ነገር በሙሉ መረጃዎች አጠናቅረው ዶሴ አዘጋጅተው ሌላው ቀርቶ ኢህአዴግ አካባቢውን ከተቆጣጠረበት ግዜ አንስቶ ጠቅላላ ጉባኤው እስከተደረገበት ወቅት ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ የተገደሉ ሰዎችን ስም ዝርዝር እስከ አያታቸው መዝግበው ይዘዋል፡፡
የ2007 ምርጫ ለኢህአዴግ በክልላቸው የመጨረሻ እንደሚሆን በድፍረት የሚናገሩት እነ አብርሃም ምርጫው ከመድረስ አስቀድሞ ምርጫ ቦርድ የተባለ መራጭ አንድነትን ለትዕግስቱ መስጠቱን ተከትሎ ህልማቸው ተዘረፈ፡፡አፍታም ሳይቆይ የአብርሃም አካባቢ የአንድነት አባላት በገዢው ፓርቲ ፖሊሶች ታስረው ማዕከላዊ ተወሰዱ፡፡
አብርሃምና ከአፈናው የተረፉት የአርማጭሆ ልጆች ተማከሩ፡፡ከአሁን በኋላ ምን ቀረን የሚለው ጥያቄ የምክራቸው ማጠንጠኛ ነበር፡፡ፓርቲያቸው ፈርሷል፣ሰላማዊ ትግልን የቆረቡበት ያህል ጸንተው ያጸኗቸው ጓዶቻቸው ‹‹ሽብርተኛ››ተሰኝተው ደብዛቸው እንዲጠፋ ተደርጓል፡፡እናማ ቀሪዎቹን የወሰዱ እግሮች እያንዳንዳቸው ደጃፍ ከመድረሳቸው አስቀድሞ ቀደሟቸው፡፡
አብርሃምን በምስሉ እንደምትመለከቱት በረሃ ወርዶ ከሐሳቡ ውጪ የነበረውን መንገድ ተቀላቅሏል፡፡ከ15 የማያንሱ የጎንደር አካባቢ የቀድሞ የአንድነት አባላትም ዛሬ በአብርሃም መንደር ይገኛሉ፡፡

No comments:

Post a Comment

wanted officials