Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Sunday, January 8, 2017

የአፍሪካ ሻምፒዮን ብሎ ሰለሰየማቸው ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሁለት ሁለት አውቶቡስ ሸለማቸው

የሱዳን መንግስት ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሁለት አዉቶቡሶችን ለገሰ
ባለፈዉ ሰኔ የሱዳኑ ፕሬዚደንት ኡመር አልባሽር የአፍሪካን የክብር ሻምፒዮን ተብለዉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በኔልሰን ማንዴላ አዳራሽ ዉስጥ ተካሒዶ በነበረዉ የአፍሪካ የክብር ሻምፒዮን ፎረም ላይ በተካሔደዉ የሽልማት ሥነ ስርዓት ላይ ሽልማቱን በተቀበሉበት ጊዜ በገቡት ቃል መሰረት እንደሆነ ታዉቋል። 
Image may contain: outdoor
በርክክቡ ላይ አዲስ አበባ የሚገኘዉ የሱዳን አምባሳደር የሆኑት አምባሳደር ጀማል አል ሸኪህ አሕመድ እንደተናገሩት ስጦታዉ የሚያመላክተዉ በሁለቱ አገሮች ለረጅም ጊዜ አብሮ የኖረዉን የአብሮ መኖርና በጋራ መሥራትን የሚያመላክት ነዉ ብለዋል። አሕመድ እንዳሉት ኢትዮጵያና ሱዳን ታሪካዊ ወዳጅነት ያላቸዉ እንደመሆናቸዉ በሁለቱ አገራት ዩኒቨርስቲዎች ዉስጥ ያለዉን የባሕል ልምድ ልዉዉጥ በማክበር ለወደፊትም አጥብቀዉ እንደሚሰሩበት ገልፀዋል።
የአዲስ አበባዉ ዪኒቨርስቲ ፕሬዚደንት የሆኑት ፕሮፌሰር አድማሱ ፀጋዬ በርክክቡ ላይ ባደረጉት ንግግር እነዚህ አዉቶቡሶች ዩኒቨርስቲያቸዉ ያለበትን ችግር እንደሚያቀልላቸዉ በተለይ ወደ ኢንዱስትሪ እና የቢዝነስ ተቋማት ፊልድ ለመሄድ የነበረባቸዉን ችግር እንደሚያቃልል ገልጿል።  እንደ ዩኒቨርስቲዉ ፕሬዚደንት ገለፃ በሁለቱ አገሮች ዩኒቨርስቲዎች እና ሌሎች ክፍተኛ ተቋማት መካከል ሊኖር ስለሚገባዉ ትብብር እየሰሩም እንደነበር ገልፀዋል።
የሱዳኑ ፕሬዚደንት ኡመር ሐሰን አልባሽር እነዚህን አዉቶቡሶች ለመስጠት ቃል ገብቶ የነበረዉ የአፍሪካ የክብር ሻምፒዮን ተብለዉ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በሚገኘዉ የኔልሰን ማንዴላ አዳራሽ ዉሰጥ በተካሔደዉ የሽልማት ስርዓት ላይ በተሸለሙበት ጊዜ እንደነበር ሪፖርቱ አያይዞ ገልጿል። የሱዳን ትሪቡን እያንዳንዱ አዉቶቡስ 50፣000 ዶላር ሊያወጡ እንደሚችሉም በዘገባዉ አካቷል።-

No comments:

Post a Comment

wanted officials