Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Saturday, January 14, 2017

ጥምቀት 2009 በጎንደር በአጥቢያ ቤተክርስቲያን እንጂ በአደባባይ እንዳይከበር የቀረበ ጥሪ


ወያኔ ኢህአዴግ አሁን ከሚገኝበት የቅዠት መፍጨርጨር እንደነዚህ ያሉ በዓላትን በግብረ በላዎቹ አዘጋጅነት እንዲከበሩ በማድረግ ለእድሜው ማራዘሚያ ለመጠቀም እንጅ ለኢትዮጵያዊያንም ሆነ ለኢትዮጵያ በማሰብ አይደለም።
ወያኔ ከመነሻው ኢትዮጵያን በተለይ ኢትዮጵያ ማለት አማራ ነው በሚል የተንሸዋረረ አስተሳሰብ አማራን በቀንደኛ ጠላትነት በመፈረጅ የአማራ ዘርን በማያወላውል ጭካኔ ለማጥፋት ያለ አቅሙን እየተጠቀመ ይገኛል። ሞረሽ አማራ ምስጋና ይድረሳቸውና እኛ ከምናውቀው በመጨመር መረጃን መስረት አድርገው ለዓለም ህዝብ አሳይተውልናል። በዚህ አጋጣሚ ይህን አውነትና ሀቅ እንዲታይ የደረጉትን ኢሳትንም እናመሰግንአለን።
ወያኔ የአማራ ተፈጥሮአዊ መንፈሳዊ ባህላዊና ታሪካው ሀብት፦ ፈጣሪ በአካል በአምሳሉ ከፈጠረው ሰው ጀምሮ ፍጥረታትን ከማጥፋት ጀምሮ ቢችሉ ስነ ምህዳሩንም ለማንቀሳቀስና ለማዛባት ከሞከሩአቸው፦
1. የአምላክ የተፈጥሮ ስጦታዎች ከሆኑት የአማራ ክልል ሀብቶች በዓለም አጅግ የሚታወቀውን የዓባይ ፏፏቴ ባለሙያዎች ፏፏቴው እያለ የኢልክትሪክ ኃይል ማመንጨት መቻሉን ይህ የማይቻል ቢሆን እንኳን ፏፏቴው ከቱሪዝም የሚያስገኘው ገቢ የታሰበውን ኃይል በእጠፍ ማስገዛት የሚችል መሆኑን ቢያሳዩ ከውስጣቸው ሰንቀውት በመጡት አማራ ከነሀብቱ የማጣፋት እቅዳቸው የዓባይ ፏፏቴን ለማጠፋት የሚቻላቸውን ሁሉ አድርገዋል።
2. የሰሜን ተራራን በአፀደቁትና በአሰሩት የመሬት አመላካች ካርታ ወደ ትግራይ በማካለል የማስተማሪያ መፃህፍት አዘጋጅተው ትውልዱ እየተለማመደው እንዲቆይ ሲሰብኩ የጎንደር አማራ ኢትዮጵያዊያን አመፅ ጉረሮአቸው ሲያንቃቸው ከአርባ ምንጭ በመጣ እውቅት በሌለው ሰው ሰለተዘጋጀ ነው ብለው መፃህፍቱን በማጥፋት ሲያምታቱ አጅ ከፍንጅ ተይዘዋል።
3. ሰው ሰራሽ የላሊበላ ቅርሳችን የትግራይ ክልል ሀበት ነው በማለት በዓለም ገበያ ሲያስተዋውቁ ተገኝተዋል። ከዚህ በተጨማሪም በሌሎቹ የአማራ ክልል አብያተ ከርስቲያናት የትግሬ አገልጋይ በመመደብ ዝረፊያ ለማካሄድ ሲያመቻቹ ከቆዩ በኃላ ከቅረብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ለቅርሶቹ ደህንነት በሚል ማታለያ ወደ አክሱም ሊውሰዱ ትዕዛዝ ሲያስተላለፉ ተይዘዋል። የየአካቢው ህበረተሰብም ሌት ከቀን እየጠበቀ ይገኛል።
4. ከጥንት ጀምሮ የተከበረና ገናና ታሪክ ያለው በውስጡ አፈር ጭረው ቅጠል በጥሰው የሚኖሩ የበቁ አባቶችና እናቶችን የያዘውን አንድ የሴቶች አምስት የወንዶች በድምሩ ስድስት ገደማት ያቀፈውን የዋልድባ ገዳም ለማጥፋት ያድረጉት ግፍ ታምራቱ የኃጢያት መሪያቸው ሳጥናኤል መለስን ባለተጠበቅ ስዓት ማጣታቸው እንኩዋን ትምህርት አለሆናቸው ብሎ አሁንም ድረስ ትግሉ ሳይበርደ እንደቀጠለ ይገኛል።
5. ከማይዳሰሱ ባህላዊ ቅርሶቻችን ለምሳሌ አሸንድዮ በስፋት በሚበቅልበት በአማራ ክልል ባሉት ከፍተኛ ቦታዎች ሰቆጣ ሰሜን ደቡብ ወሎ ደቡብ ጎንደር ምስራቅ ጎጃም በመላው አማራ የሚከበር ባህል መሆኑ እየታወቀ ወያኔ በማንአለብኝነትና ውሸት አሻንድየ የትግራይ ብቸኛ ባህል ነው በሚል በዩኒስኮ በትግራይ ስም ለማስመዝገብ በመፍጨርጨር ላይ ይገኛሉ።
6. አሁን የዚህ ሀሳብ መነሻ የሆነውና ዓለም የሚያውቀውን ኃይማኖታዊና መንፈሳዊ ጥምቀት በጎንደር በዓል ከትልቅ እሰከ ትንሽ ሁላችንም ተከባብረን ድንቡሎ ሳቲም ሳይጠፋ ደንገት ወድቃ ብትገኝ እንኳ የኃይማኖት አባቶች በድምፅ ማጉያ ጠርተው ለባለቤቱ እየደረሰ በፍፅም ኢትዮጵያዊነት የሚከበር ባዓላችን መሆኑ ይታወቀል። ሆኖም ባለፋት 10 ዓመታት ውስጥ ግን የትግራይን ወጣቶች ወደ ጎንደር በማስገባት በኪስ አውላቂነት እያደረጉት ያላው ጥምቀት በጎንደር ገፅታ የማበላሸት እንቅስቃሴ የጎንደር ከተማ ፖሊስ ጣቢያዎችና የጣቢያዎቹ የእለት ሁኔታ መመዝገቢያዎቹ በሆድ አደሮች ካልተሸሸጉ በሰተቀር ያስረዳሉ።
ስለዚህ ከላይ የተዘረዘሩትን ወንጀሎች ከሚፈፅም መንግሰት ነኝ ባይ ጋር የጥምቀትን በዓልን ማክበር እራስን አለማወቅ ከመሆኑ በተጨማሪ ለሐገር ነፃነት የተዋደቁ ውድ የጎንደር ልጆች ሲሳይ ታከለ ሻለቃ ማሰፍንት አቶ ሰጠኝና ከኢሬቻ በዓል በፊትና በኃላ የተገደሉ የኦሮሞ ወገኖቻችን አሁንም በቤኒሻንጉል አኝዋክ ጋምቤላ የሞቱና እየተገደሉ ያሉ ወኖቻችን መርሳት ትልቅ ክህደት በመሆኑ የነዚህ ወገኖቻችን ደም ድምፅ አውጥቶ እንዳንሰማው አፅማቸው አንዳይወቅሰን።
ከዚህ በተጨማሪ ለሰው ግድ የለለው ወያኔ ባለፈ በኤሬቻ በዓል እንደጨረሳቸው የኦሮሞ ወገኖቻችን አሁንም በተለይ እኛን ጎንደሬ አማሮች በአንድ ላይ አግኝቶ ለመግደል የተለመደ የሌብነት ስራ የሚሰሩትን የትግራይ ወጣቶች በጠብ ጫሪነት በማሰማራት ለመፍጀት አቅዶ እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ስለደረስንበት። ለዚህ አረመኔአዊ የወያኔ እቅድ ተጋላጭ በመሆን ጀግና ወላድ የጎንደር እናትና አባቶቻችን እንዳናስለቅስና አንገት እንዳናስደፋ ጥምቀት በጎንደር 2009 ለማክበር እንዳንወጣና በቤታችን እንድንውል ከወዲሁ ጥብቅ ምክር አዘል መልዕክታችን አናስተላለፋለን።
ቀሳውስት የይሐማኖት አባቶቻችንም በመስቀል የተደገሰልንን እንደፍሪዳ የመታረድ ድገስ በፍፁም ኃይማኖታዊ አባትነት ታደጋችሁ አድናችሁናል። አሁንም ”እረኝነታችሁን ዘንግታችሁ በጎቻችሁን በተኩላ እንዳታስነጠቁ” የሚለውን የአምላካችን ቃል ጠብቃችህ ታቦቶችን በማውጣት ጎንደርን ለደም መፍሰስ እንዳታጋለጥ ታደርጉ ዘንድ አየተማፀን። ይህ ህይወታችሁን አስከሚያሳጣችሁ ማስፈራራት ድረስ ቢሄድ እንኳን እንደ አባታችን አቡነ ጴጥሮስ መስቀላቸሁን ይዛችሁ ”መላዕክታንና ሰማዕታት ከፊታችሁ ከጎናችሁ ከኃላችሁ እንደቆሙ በማመን” ፈጣሪያችን ሳትጠራጠሩ መስዋዕት በመሆን የሚጠበቅባችሁን የሰማዕትንት ስራ እንድትሰሩ በልጅንት አክብሮት እንጠየቃችሁአልን።

No comments:

Post a Comment

wanted officials