Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, February 12, 2015

በፕሮፓጋንዳው ስራ በኩል በሚታየው ድከመት ዙሪያ የመንግስት ሹመኞች እርስ በርሳቸው ተካሰሱ


ኢሳትዜና :-በቅርቡ በኪሚኒኬሽን ሚኒስትሩ ሬድዋን ሁሴን በተመራው የቀድመው ኢቲቪ የአሁኑ ኢቢሲ አመራሮች፣ የፕሬስ መምሪያ ሃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ ሬዲዮ አመራሮች፣ የህዝብ ግንኙነቶች፣ ኮሚኒኬተሮችና ሌሎች ባለስልጣናት በተገኙበት በተካሄደው ውይይት ላይ የመንግስት የህዝብ ግንኙነት ሰራተኞች የአትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋዜጠኞችን ሲከሱ፣ የኢቢሲ አመራሮች ደግሞ ረጃጅም እጆች ያሉዋቸው ባለስልጣናት ቴሌቪዥኑን ስለተቆጣጠሩት ፍትሃዊ የሆነ ሽፋን ለመስጠት አልተቻለም ሲሉ ወቅሰዋል።
“ረጅም እጅ ያለው ባለስልጣን ካለ፣ ሄክታር መሬትም ቢታረስ ስድስት ጊዜ ዜና ይሰራለታል” በማለት በቅርቡ የተሾሙ የኢቢሲ ባለስልጣን ተናግረዋል
ሌላ ሃላፊ ደግሞ መንግስት በፕሮፓጋንዳው መስክ አጀንዳ ቀርጾ መስጠት አለመቻሉን፣ ከውጭ ተቀርጾ ለሚመጣ አጀንዳ መልስ በመስጠት ላይ ማተኮሩን፣ የህዝብ ግንኙነት ስራው ከአጥቂት ይልቅ ተከላካይ መሆኑንና በማህበራዊ የመገናኛ ብዙሃን አጀንዳ እየቀረጸን ከመከላከል ይልቅ ማጥቃት አለብን ” ብለዋል።
በክልል ጋዜጠኞች መካከል መግባባት እንደሌለ፣ አንዱ ክልል የሌለው ክልል ጉዳይ እንደማይመለከተው፣ የክልል ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የፌደራል ጉዳይም አይመለከተንም ብሎ በክልል የመገናኛ ብዙሃን ዘገባዎች እንደማይቀርቡም ተገልጸሏል
ሚኒስትሮችን ጨምሮ አመራሮች ፌስ ቡክ ቢከፍቱም ፣ የፎቶ አልበም ከመለጠፍ ውጭ የሚሰሩት የለም በማለት አማረው የተናገሩት ሌላ ባለስልጣን፣ ከክልሎች የአማራ ክልል በፌስ ቡክ አጠቃቀም ተሽሎ መገኘቱን ተናግረዋል።
ለኢሳት በደረሰው ሚስጢራዊ የድምጽ ማስረጃ የትግርኛ ክፍል ጋዜጠኞች ደግሞ የአቶ ሃይለማርያምን ቃለምልልስ በመተርጎም፣ እንዲሁም መኢአድና አንድነት ሲለያዩ ዜናውን በደንብ አጉልታችሁ አልዘጋባችሁም ተብለው ሲጨቃጨቁ ይሰማል።
አቶ ሽመልስ ከማልና አቶ ሬድዋን ሁሴን የአሸባሪው ቡድንን የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ መመከት የሚቻለው በጋራ መስራት ሲቻል ብቻ ነው በማለት የተለያዩ ምክሮችን ሰንዝረዋል።
ኢህአዴግ ለፕሮፓጋንዳ ስራ በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ በእያመቱ እንደሚያወጣ ይታወቃል።
ስብሰባው ላይ ስለተነሱት ጉዳዮች ሙሉ ዝግጅቱን በቅርቡ እናወጣዋለን።

No comments:

Post a Comment

wanted officials