Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Friday, February 6, 2015

በመከፋፈል እና በመገነጣጠል ተግባሩ የቀጠለው ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ ከወሎ ተጨማሪ መሬት ለመከለል ዝግጅት ላይ መሆኑ ታወቀ!

ከተመሰረተ 40 አመት ሊያስቆጥር ቀናት የቀረውና አሁንም በገንጣይነት ተግባሩ የቀጠለው ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ ከወሎ ተጨማሪ መሬት ለመከለል ዝግጅት ላይ መሆኑ ታወቀ፡፡ ለደሴ ሆስፒታል ባዛር በተደረገበት ወቅት ህወሓት አገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ የትግራይ ተወላጅ ባለሀብቶች በባዛሩ እንዲገኙ ያደረገ ሲሆን በወቅቱም ወሎ ውስጥ ሰፊ መሬት እንዲሰጣቸው አድርጓል፡፡ በተለይም ከቆቦ ወደ ወልደያ በኩል 35 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው አላውሃ የተባለ ቦታ ላይ በርካታ የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ደጋፊና አባል ባለሀብቶች መሬት ተሰጥቷቸዋል፡፡ ውስጥ ለውስጥም ‹‹የትግራይ ድንበር አላውሃ ምላሽ ነው›› በሚል እያስወራ እንደሚገኝ የአካባቢው ነ…ዋሪዎች ገልጸዋል፡፡አላውሃን ጨምሮ ሌሎች የትግራይ ድንበር አካባቢ የሚገኙ የወሎ መሬቶች ላይ አርሶ አደሮቹን እያፈናቀሉ ለህወሓት ደጋፊና አባል ባለሀብቶች መሬት ለመስጠት ሰፊ እቅድ እንደተያዘና በሂደት በአካባቢው በርከት ያሉ ትግርኛ ተናጋሪዎች እንዲኖሩ በማድረግ ቦታውን ወደ ትግራይ ለመከለል ሴራ እየተሸረበእንደሚገኝ የውስጥ ምንጮች ገልጸዋል፡፡የቆቦና ሌሎች የትግራይ ድንበር አካባቢ የሚገኙ የወሎ መሬቶች ላይ በርካታ የትግራይ ተወላጆች ተሰጥተው የአካባቢው ተወላጆቹ መሬት አልባ መሆናቸው ይታወቃል፡፡ ይህም ተከትሎ ሰሞኑን ወሎ ውስጥ ተጨማሪ መሬቶች ወደ ትግራይ ሊከለሉ ነው በሚል ህዝቡ ውስጥ ከፍተኛ ውጥረት ተፈጥሯል፡፡ ህወሓት ስልጣን ከያዘ ጀምሮ የጎንደርና የወሎ መሬቶችን ወደ ትግራይ መከለሉ የሚታወቅ ሲሆን በቅርቡ በስፋት የጀመረው መሬትን ለትግራይ ባለሀብቶች የመስጠት እቅድም ወደፊትም ሰፋፊ መሬቶችን ወደ ትግራይ ሊከልል እንደሚችል አመላክቷል፡፡

No comments:

Post a Comment

wanted officials