Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, February 3, 2015

የምርጫ ቦርድ የፓርቲዎች ሚዲያ አጠቃቀም ድልድል ፍትሃዊ አለመሆኑን ሰማያዊ ፓርቲ ገለጸ

የምርጫ ቦርድ የፓርቲዎች ሚዲያ አጠቃቀም ድልድል ፍትሃዊ አለመሆኑን ሰማያዊ ፓርቲ ገለጸ

ጥር ፳፭(ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰማያዊ ፓርቲ የምርጫ ቦርድ ያወጣው ረቂቅ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ውድድር የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ሰዓት አጠቃቀም ድልድል ፍትሃዊና በእኩልነት ላይ የተመሰረተ አለመሆኑን አስታውቋል።
ነገረ ኢትዮጵያ እንደዘገበው ጥር 25 ቀን 2007 ዓ.ም የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሀገር አቀፍ ፓርቲዎችን በረቂቅ የሰዓት ድልድሉ ላይ ጊዮን ሆቴል ጋብዞ ውይይት አድርጓል፡፡
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን  ኃላፊዎች ባቀረቡት የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚዲያ አጠቃቀም ረቂቅ ድልድል መሰረት 55 በመቶ በፓርላማ መቀመጫ ወንበር ላላቸው ፓርቲዎች፣ 20 በመቶ ፓርቲዎቹ በሚያቀርቧቸው ዕጩዎች ብዛት እንዲሁም ቀሪ 25 በመቶ ለሁሉም ፓርቲዎች በዕኩል የሚከፋፈል እንደሆነ ተገልጿል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲን በመወከል በውይይቱ ላይ የተገኙት የፓርቲው የህግ ጉዳይ ኃላፊ አቶ ይድነቃቸው ከበደ  የሚዲያ ሰዓት አጠቃቀም በሚቀርቡ እጩዎች ብዛት እና በእኩልነት የሚከፋፈል የድልድል መስፈርት መሆን ሲኖርበት የፓርላማ መቀመጫ እንደመስፈረት መቀመጡ ትክክል አለመሆኑን ለኢሳት ገልጸዋል ኢህአዴግ የድልድሉ መስፈርት ላይ እንደሚስማማ በመግለጽ፣ በመቶ የተቀመጠው መጠን ላይ ግን መሻሻል እንዲደረግ እንደሚፈልግ መግለጹንም ነገረ ኢትዮጵያ ዘግቧል፡፡

No comments:

Post a Comment

wanted officials