Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, February 24, 2015

በአዲስ አበባ የታክሲ ሹፌሩ መኪናውን አቁሞ ራሱን ወደድልድዩ ወርውሮ ሕይወቱን አጠፋ (ፎቶዎች ይዘናል)


በአዲስ አበባ የታክሲ ሹፌሩ መኪናውን አቁሞ ራሱን ወደድልድዩ ወርውሮ ሕይወቱን አጠፋ (ፎቶዎች ይዘናል)





አዲስ አበባ ያሉ የዘ-ሐበሻ ተከታታዮች “እኔም የዘ-ሐበሻ ሪፖርተር ነኝ” ካሉን ቆይተዋል:: በሶሻል ሚዲያ ለዘ-ሐበሻ መረጃዎችን በፎቶ አስደግፈው መላካቸውን ቀጥለዋል:: አሁንም ለሌሎች ኢትዮጵያ ውስጥም ሆነ በሌሎች ሃገራት የሚገኙ የዘ-ሐበሻ ወዳጆች ‘እኔም የዘ-ሐበሻ ሪፖርተር ነኝ’ በማለት መረጃዎችን በቶሎ በሶሻል ሚዲያዎቻችን በፌስቡክ, ዋትሳፕ, ቫይበር, ስካይፕ, ትዊተር እና ሌሎችም መንገዶች ሊያደርሱን ይችላሉ::

ዛሬ የአዲስ አበባ የዘ-ሐበሻ “ሪፖርተር” 6 ፎቶ ግራፎችን ከመረጃ ጋር አድርጎ ልኮልናል:: እንደመረጃ ምንጫችን ገለጻ ድርጊቱ የተፈጸመው በአዲስ አበባ በተለምዶ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን አካባቢ ነው:: ትናንት ከቀኑ 8:45 አካባቢ እስጢፋኖስ ቤ/ክ አካባቢ የሚገኝ ድልድይ ጋር የሚነዳትን ታክሲ በማቆም ወደ ወንዙ ራሱን በመወርወር ራሱን አጥፍቷል:: በፎቶዎቹ እንደምታዩት ፖሊስ ጉዳዩን ሲከታትልና የወደቀውን ታክሲ ሾፌር ነው:: የታክሲ ሹፌሩ ለምን ራሱን እንዳጠፋ በምርመራ ላይ ሲሆን ለጊዜው የተገኘው መረጃ ራሱን ማጥፋቱ ብቻ ነው::

ፎቶዎችን ይመልከቱ:: እርስዎም የዘ-ሐበሻ ሪፖርተር ይሁኑ::






-source:
 See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/39217#sthash.NjASBSgU.dpuf

No comments:

Post a Comment

wanted officials