(ዘ-ሐበሻ) የአዲስ አበባ ሕዝብ “ባቡሩን ሳንሄድበት አደጋ ጨረሰው” ማለት ጀምሯል:: ከሁለት ሳምንት በፊት የተመረቀውና ሥራ የጀመረው የአዲስ አበባ ባቡር ሃዲድ አጥር ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ ላይ የመኪና አደጋ ማስተናገዱን ዘ-ሐበሻ መዘግቧ አይዘነጋም:: ዛሬም ከአዲስ አበባ በፎቶ ግራፍ ተደግፎ ያገኘነው መረጃ “ባቡሩን ሳንሄድበት የመኪና አደጋ ጨረሰው” ያስብላል:: በፎቶ ግራፍ እንደምታዩት ይህ ገልባጭ መኪና የባቡሩን አጥር ሰብሮ ገብቶበታል:: ወደ ሳሪስ መሄጃ ጎተራ ማሳለጫው እንደተሻገረ ነው መኪናው አደጋውን ያደረሰው:: እንዴት እንዲህ ያሉ ትላልቅ መኪናዎች በጠባብ መንገድ እንዲያልፉ ይፈቀዳል? መልሱን ለሕወሓት/ኢሕአዴግ የመንገድ ባለስልጣን ትተነዋል::


No comments:
Post a Comment