Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, February 24, 2015

ተወዳድሮ ማሸነፍ የሚችለው ሰማያዊ ብቻ መሆኑ ተረጋገጠ


ተወዳድሮ ማሸነፍ የሚችለው ሰማያዊ ብቻ መሆኑ ተረጋገጠ



ነገረ ኢትዮጵያ

መድረክ 218 ኢዴፓ 127 መቀመጫዎች ብቻ ነው ያሰመዘገቡት





የምዝገባ ጊዜ ሳይጀምር፣ የአንድነት ፓርቲ ከሶማሌ ክልል በስተቀር በሁሉም የአገሪቷ ክፍሎች ለፓርላማና ለክልል ምክር ቤቶች ተወዳዳሪዎች አዘጋጅቶ እንደነበረ ይታወቃል። የአንድነት ጥንካሬ ከወዲሁ የተረዳሁ የሕወሃት ፖሊት ቢሮ ለምርጫ ቢርድ መመሪያ በመስጠት፣ ተለጣፊ ቡድን በማደራጀት አንድነት ላይ የኃይል እርምጃ ወስዷል።


የአንድነት አባላታ ለድርጅት ሳይሆን ለነጻነት የሚታገሉ እንደመሆናቸው ማሊያ ቀይረው በሰማያዊ ፓርቲ ሥር ለመንቀሳቀስ ተነሱ። የሰማያዊውች እና የአንድነቶች መያያዝ ትግሉን የበለጠ አጠናከረው። ሳምንታ ባልሞላ ጊዜ ዉስጥ አንድነቶ ተነቃነቁ። ወደ ሰማያዎ ጎረፉ። በፊትም ጠንካራ የሆነው የሰማያዊ ፓርቲ አንድነቶች ሲመጡ የበለጠ ተጠናክሮ ከአራት በላይ ለፓርላማ፣ ከሰባት መቶ በላይ ለክልልተወዳዳሪዎች አስመዘገበ። ከሁለት መቶ በላይ የሚሆኑ ተወዳዳሪዎች በምርጫ ቦርድ የሌላ ፓርቲ አባል ናችሁ በሚል ተሰረዙ።

እንደዚያም ሆኖ ከኢሕአዴግ ቀጥሎ ብዙ ተወዳዳሪዎችን ሰማያዊ ፓርቲ እንዳሰለፈ ለማወቅ ተችሏል። ኢሕአዴግ ከ547 የፓርላማ መቀመጫዎች 457 ላይ ተወዳዳሪዎች ያስመዘገበ ሲሆን፣ ሰማያዊ የተሰረዙትን ሳይጨመር ለፓርላማ 345 (63%) ተወዳዳሪዎችን አስመዝግቧል። ኢሕአዴግ የሚወዳደረው በትግራይ፣ ደቡብ፣ አማራና ኦሮሚያ ክልልም በአዲስ አበባ ብቻ ነው። በአፋር፣ ሶማሌ፣ ቤኔሻንጉልና ጋምቤላ የሚወዳደሩ ኢሕአዴግ አጋር ድርጅቶች የሚላቸው ናቸው።፡

የብዙ ድርጅቶች ስብስብ የሆነ መድረክ 218 ( 39%) መቀመጫ ብቻ ሲሆን ለፓርላማ ያሰለፈው በትግራይ ከ38 መቀመጫዎች ከሰላሳ በላይ፣ በኦሮሚያ ከ175 መቀመጫዎች በ160ው ተወዳዳሪዎችን አሰልፏል። በደቡም ክልል ወደ ሃያ ብቻ የሚሆኑ ተወዳዳሪዎችን ያሰለፈ ሲሆን በአማራዉ ፣ በጋምቤላ፣ በአፋር፣ በቤኔሻንጉልና በሶማሌ ክልል ምንም ተወዳዳሪዎችን አላስመዘገበም።
ከመድረክ ቀጥሎ ብዙ ቁጥር ያስመዘገበው ኢዴፓ ሲሆንም ፣ ለ127 መቀመጫዎች (23%) ተወዳዳሪዎችን አስመዝግቧል።

በዚህ መሰረት ገዢው ፓርቲ ድምጽ መስረቁ አይቀርም እንጂ፣ ካሰመዘገባቸው 345 የፓርላማ አባላት 274 ቱን ( 80% ) ማሸነፍ ከቻለ ስልጠና የመያዝ እድል ይኖረዋል። እንድ እመድረክ፣ ኢዴፓና ሌሎች ያሰለፏቸውን በሙሉ መቶ በመቶ ቢያሸንፉም ስልጣን መያዝ አይችሉም።

No comments:

Post a Comment

wanted officials