Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Saturday, February 14, 2015

በትግራይ ቀንደኛ የህወሃት ካድሬ ተገደለ

መረጃ ለነፃነት
ኮረም ከተማ ውስጥ ህዝቡን እያሰቃየ የቆየው አንድ የስርዓቱ ካድሬ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ተገድሎ ማደሩን የተገኘው መረጃ አስታወቀ።
ከተማው ውስጥ የሚገኙ ምንጮች አንደ ገለፁት በትግራይ ደቡባዊ ዞን የኮሮም ከተማ ነዋሪ የሆነው የዋግነህ በለጠ የተባለው ካድሬ ጥር 21/2007 ዓ/ም ሌሊት ላይ ከኮረም ወደ አላማጣ በሚወስዶው መንገድ ላይ በስለት ተወግቶ ህይወቱ አልፎ ማደሩ ታውቋል።
የሞተው ሚልሻ የስርዓቱ ዋንኛ ታማኝ እንደነበረና ህዝቡን እያሰቃየ መቆየቱን የገለፀው መረጃው የአካባቢው ተወላጆች የበቀል እርምጃ እነደሚወስዱበት እየዛቱ መቆየታቸው ታውቋል። የመከላከያ ሰራዊት ሚልሻው ሞቶ ባገኙበት ሰዓት እስከሬኑን ለምርመራ መቐለ ድረስ መውሰዳቸውና በተጨማሪም የከተማው ፖሊስ ከሟቹ ጠብ ነበራቸው ያላቸውን ንፁሃን ወገኖች በጥርጣሬ እያሰሯቸው መሆኑን መረጃው አክሎ አስረድቷል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials