Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Monday, December 26, 2016

ብሪታኒያ በደቡብ ሱዳን ተጨማሪ 400 ወታደሮችን የማሰማራት እቅድ እንዳላት ገለፀች።


የአገሪቱን ከፍተኛ ባለስልጣናት ጠቅሶ ሲሲቲቪ እንደዘገበው፥ አሁን የሚላኩት ወታደሮች በዚያ የሚገኘውን 12 ሺህ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰላም አስከባሪ ጦር ለማጠናከር ነው።
ወታደሮቹም በብዛት የህክምና እና ምህንድስና አገልግሎት የሚሰጡ እንደሚሆንም ነው የተመለከተው።
ደቡብ ሱዳን ከፈረንጆቹ 2013 ታህሳስ ወር ጀምሮ ጦርነት ላይ ትገኛለች።
ይህን ግጭት ለማስቆም በፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር እና በተቀናቃኛቸው በኩል የሰላም ስምምንቶች ሲፈረሙ ቢቆዩም በተደጋጋሚ ሲፈርሱ ታይትዋል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተሰናባቹ ዋና ፀሃፊ ባን ኪሙን ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ፈጥኖ ለዚያች አገር ቀውስ ምላሽ ካልሰጠ የከፋ ጥፋት እንደሚደርስ አስጠንቅቀዋል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials