Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Monday, December 26, 2016

ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ ነገ ፍርድ ቤት እንደማይቀርብ ታወቀ

ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ በ2006ዓ.ም ዕንቁ መጽሔት በዋና አዘጋጅነትበሚሰራበት ወቅት የመጽሔቱ አምደኛ የሆነውን ሰዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን ጽሑፍ በሆነው ‹‹የተገነቡትና በመገንባት ላይ ያሉ ሃውልቶች የማንና ለማን ናቸው)›› በሚል ርዕሥ የተጻፈ ጽሑፍ በጅማ ዩኒቨርሲቲ በተማሪዎች መካከል ብጥብጥ ተነስቶ ወደ 40.000 ብር የሚገመት ንብረቶች ወድሟል›› ሲል የፌዴራል አቃቤ ሕግ ባቀረበው ክስ ምክንያት በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ሁለቱም ተከሳሾች ይቀርባሉ፡፡አቃቤ ሕግ ‹‹ግዙፍ ባልሆነ የወንጀል ድርጊት የሀገሪቷን ህዝቦች አንድነት ለመለያየት በማሰብ›› የሚል ይዘት ያለው ክስ ያቀረበ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ፍርድ ቤቱም ሰዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳንና ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩን እያንዳንዳቸው የ20.000 ሺህ ብር ዋስትና ተጠይቆባቸው በወቅቱ የተጠየቀውን የዋስትና ማስያዝ ባለማቻላቸው ምክንያት ለአንድ ሳምንት ያህል በቂሊንጦ እስር ቤት ከታሰሩ በኋላ የዋስትና ማስያዟው በሰዎች ትብብር ተከፍሎ ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ እና ሰዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን በቀጠሯቸው ቀን እየተገኙ በመከራከር ላይ ይገኛሉ፡፡ ፍርድ ቤቱም የመከላከያ ምስክሮችን ለመስማት ታኅሳስ 19 ቀን 2009ዓ.ም የቀጠረ ቢሆንም የቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩን ፍርድ ቤት እንደማያቀርበው ለማወቅ ተችሏል፡፡
ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ በተለያዩ የግል ጋዜጦች ላይ የሰራ ሲሆን በ‹‹አውራምባ ታምይስ›› እና በ‹‹ፍትህ›› ጋዜጦች ላይ በከፍተኛ ሪፖርተርነት፣ በ‹‹ዕንቁ›› መጽሔት እና›› ‹‹በቀዳሚ ገጽ›› ጋዜጦች›› ‹‹በአዲስ ገጽ መጽሔት›› በዋና አዘጋጅነት የ‹‹ሚሊዮኖች ድምጽ›› ጋዜጣ በምክትል አዘጋጅነት የሰራ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት በኮማንድ ፖስቱ በቦሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ ከአንድ ወር በላይ ታስሮ የሚገኝ ሲሆን ኮማንድ ፖስቱ ፍቃድ ካልሰጠ በስተቀር ነገ ፍርድ ቤት እንደማይቀርብም ለማወቅ ተችሏል፡፡

No comments:

Post a Comment

wanted officials