Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Wednesday, December 7, 2016

የሰማያዊ ፓርቲ ፓርቲ የምስራቅ ጎጃም ዞን ድረጅት ጉዳይ ኃላፊና የሟቹ ሳሙኤል አወቀ የቅርብ ጓደኛ እንዲሁም የትግል አጋር የነበረው ወጣት እንደግ አዳነ አርበኞች ግንቦት 7ን ተቀላቀለ፡፡

የሰማያዊ ፓርቲ ፓርቲ የምስራቅ ጎጃም ዞን ድረጅት ጉዳይ ኃላፊና የሟቹ ሳሙኤል አወቀ የቅርብ ጓደኛ እንዲሁም የትግል አጋር የነበረው ወጣት እንደግ አዳነ በ2007 ዓ.ም በተካሄደው የይስሙላህ ምርጫ ሞጣ ወረዳ ላይ ለተወካዮች ምክር ቤት የተወዳደረ ሲሆን አሁን ደግሞ የህወሓትን አገዛዝ ፈፅሞ በሰላማዊ ትግል መለወጥ እንደማይቻል አምኖ ጫካ ገብቶ ብረት አንስቷል፡፡
"ሰላማዊ ትግል አብቅቶለታል!" ሲልም ለአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ ተናግሯል፡፡
ወጣት እንደግ አዳነ በ2007 ዓ.ም የሞጣ ወረዳን ወክሎ ለምርጫ በተወዳደረበት ወቅት የህወሓት አገዛዝ ማዳበሪያ በመከልከልና ሌላም የበቀል እርምጃ በመውሰድ በገበሬ ቤተሰቦቹ ላይ በደል እንዳደረሰ ገልጿል፡፡ በምርጫው ማግስት የሞጣ ህዝብ የሰጠውን ድምፅ በጠብመንጃ ከመነጠቁ በላይ የህወሓት ደህንነቶች አፍነውት ልብሶቹን አስወልቀው መለመላውን ብርድ ላይ አቁመው በማሳደር ሰቆቃ ፈፅመውበታል፡፡
አርበኞች ግንቦት 7ን ተቀላቅሎ አሁን በረሃ ውስጥ የሚገኘው ወጣት እንደግ አዳነ "ከንቱ መሰዋዕትነት ከመክፈልና ጊዜ ከመፍጀት ውጭ ፈፅሞ ለውጥ ማምጣት ስለማይቻል ከተማ የቀራችሁ የሰላማዊ ትግል ጓዶቼ በሙሉ ፈጥናችሁ የእኔን ፈለግ እንድትከተሉና ትክክለኛውን የትግል አማራጭ እንድትይዙ፡፡" ሲል ጥሪውን አስተላልፏል፡፡

No comments:

Post a Comment

wanted officials