Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, December 13, 2016

የውጭ ጉዳይ ሚ/ሩ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ በስማቸው ላይ ያደረጉትን ማጭበርበር የሚያጋልጡ ማስረጃዎች ወጡ (በማስረጃ የተደገፈ)



Ethiopiazare.com – የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ወርቅነህ ገበየሁ በፓልቶክ ክፍል ቀርቦ የኦሮሞ ተወላጅ መሆኑን አስረግጦ ተናግሯል። ካፈርኩ አይመልሰኝ ነገር።

አንድ ሰው ከመሬት ተነስቶ ከዚህ ዘር ነኝ የማለት የተጠበቀ ነው። የዘር ቆጠራን ያመጡት ራሳቸው ሥልጣን ላይ ያሉት ዘረኞች ናቸው እንጂ እኛ አይደለንም። ዛሬ የራሳቸው ቃል እስረኛ የሆኑ ይመስላል። ጥያቄው ዘሩን በገዛ ፈቃዱ የመቀየር ጉዳይ አይደለም። ተቃውሞው ሹመቱ ላይም አይደለም። በዘር ያመጡት የሥልጣን ኮታ ዘሩ ባልሆነ ግለሰብ ሲደለደል – ጉዳዩን ለሚያውቁት ንቀት እና ስድብ ይሆናል።

ወርቅነህ የኦሮሞ የገዳ ሥርዓት በሚፈቅደው ”ጉዲፈቻ” እና ”ሞጋሳ” ባህል መሰረት ወደ ኦሮሞነት ተቀይሮ ከሆነ ግልጽ ይሁን። ካልሆነ ግን የእሱን ማንነት የሚገልጸው ዶክመንት ተመልክቶ ፍርድ መስጠቱ ይበጃል።

ለስድስት ዓመታት በድህንነት ሲሠራ በርካታ ንጹሃን ዜጎችን አሳፍኗል – ከዚያም የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ሆኖ ሲሠራ በተለይ በምርጫ 97 በነበረው ጭፍጨፋ ለ200 ዜጎች ሕይወት መጥፋት ተጠያቂ ነው።
Prof. Merera on Workneh Gebeyehu
ፕ/ር መረራ ጉዲና የወርቅነህ ገበየሁ አስተማሪ ነበሩ። በዚህች አጭር ቪዲዮ ስለ ውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ የስም ማጭበርበር የሚሉት አለ። ተጨማሪ መረጃዎችን ከቪዲዮው በታች ያገኛሉ። (ለመመልከት የማጫወቻ ቁልፉን ይጫኑ!)
ማስረጃ ፩፣ ከታች ያለው የዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ የምርቃት ጥናታዊ ጽሑፍ ሲሆን፣ የአያታቸው ስም ወልደኪዳን ይላል።
Workneh Gebeyehu thesis, his grand fathers name is Woldekidan
ማስረጃ ፪፣ የምርጫ ቦርድ ውጤት ላይ የዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ የአያት ስም ነጋዎ (የኦሮሞ ስም) ኹኑዋል
Workneh Gebeyehu election board
ማስረጃ ፫፣ አዲሱ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁን አስመልክቶ ፕ/ር መረራ ጉዲና በመጽሐፋቸው ላይ ካሰፈሩት የተወሰደ።

No comments:

Post a Comment

wanted officials