Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Saturday, December 10, 2016

የአርበኞች ግንቦት 7 አመራሮች የብሄር ስብጥር ሲፈተሽ



የአርበኞች ግንቦት 7 አመራሮች የብሄር ስብጥር ሲፈተሽ
የውሸት መደጋገም ውሸትን እውነት ያስመስል እንደሆን እንጂ እንጂ ውሸትን እውነት አያደርግም
“የአርበኞች ግንቦት 7 አመራሮች ከአንድ አካባቢ በተለይ ከደቡብ የመጡ ናቸው” የሚል ማስረጃ የለሽ አሉባልታ ባለፉት ሁለት ዓመታት ሲነዛ ቆይቷል። ይህንን የተሳሳተ መደምደሚያ ለማስረገጥም የአንዳንድ አመራሮች ብሄር ተዛብቶ ተጽፎ በማኅበራዊ ሚዲያ ተሰራጭቷል። እየተባለ ያለው እውነት ይሁን አይሁን ለማጣራት በግሌ አነስተኛ ጥናት አድርጌያለሁ፤ የመሪዎቹን ጓደኞችና ዘመዶችን አነጋግሬ የደረስኩበትን እውነታ ከዚህ በታች አቀርባለሁ።
አርበኞች ግንቦት 7 ስለመሪዎቹ የብሄር ማንነት ተናግሮ አያውቅም፤ ይህ ማድረጉም ተገቢ ነው ብዬ አምናለሁ። የእውነታ መዛባት የሚያሳስበን ኢትዮጵያዊያን፣ የአግ7 ጨዋ ዝምታ ወያኔና ሌሎች የአግ7 ተቃዋሚዎች ለማጥቂያነት ሲጠቀሙበት ግን “ውሸታሞች ናችሁ” ማለት አለብን።
የአርበኞች ግንቦት 7 የስራ አስፈጻሚ አባላትና የብሄር ስብጥር፦
1. ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ (ጉራጌ)
2. አቶ መአዛው ጌጡ (አማራ)
3. አቶ መንግስቱ ወ/ስላሴ (አማራ)
4. ኮማንደር አሰፋ ማሩ (አማራ)
5. አቶ ተስፋሁን ተገኝ (አማራ)
6. ኑርጀባ አሰፋ (ደቡብ)
7. ዶ/ር ታደሰ ብሩ (ጉራጌ)
8. አቶ መሳፍንት አያሌው (አማራ)
9. አቶ ታሪኩ (አማራ)
10. አቶ ዘመኔ ካሴ (አማራ)
ሌሎች የአርበኞች ግንቦት 7 ከፍተኛ አመራሮችና የብሄር ስብጥር
1. ዶ/ር አዚዝ መሃመድ (አማራ)
2. ዶ/ር ሙሉዓለም አዳም (አማራ)
3. አቶ ታሜ (አማራ)
4. ወ/ሮ ፋሲካ (አማራና ጉራጌ)
5. አቶ ብዙነህ ጽጌ (አማራና ኦሮሞ)
6. አቶ ናእምን ዘለቀ (አማራ)
7. አቶ አበበ ቦጋለ (ኦሮሞ)
8. አቶ ቸኮል ጌታሁን (አገው)
9. አቶ ሙሉነህ እዩኤል (ከምባታና ሃዲያ)
10. አ/ቶ ኤፍሬም ማዴቦ (ከምባታ)
11. አቶ አየልኝ (አማራ)
12. አቶ ወንደሰን (አማራ)
13. አቶ ግርማቸው (አማራ)
14. አቶ ሁሉቃ (አማራ)
15. አቶ በቀለ (አማራ)
16. ወ/ሮ መቅደስ (አማራ)
17. አቶ ከፍያለው (አማራ)
18. አቶ ታደለ ወንድም (አማራ)
19. አቶ ክፈተው አሰፋ (አማራ)
ናትናኤል መኮንን

No comments:

Post a Comment

wanted officials