Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Monday, December 26, 2016

በጎንደር በህዝብ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ 10 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ

በጎንደር በህዝብ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ 10 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ

 ኢሳት ዜና :- 15 ሰዎችን ጭኖ ከጎንደር  ወደ ባህርዳር በመጓዝ ላይ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ ተሽካርካሪ ጠዳ ከተማ አካባቢ ሲደርስ በመገልበጡ 10 ሰዎች ወዲያውኑ ህይወታቸው ሲያልፍ፣ 4 ሰዎች ደግሞ በጽኑ ቆስለው ሆስፒታል ገብተዋል።
የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪው ሲኖ ትራክ እየተባለ በሚጠራ የጭነት ተሽከርካሪ ተመትቶ ሳይገለበጥ እንዳልቀረ ወኪላችን ገልጿል።
አብዛኞቹ ሟቾች ነገ የሚከበረውን ወንቅሸት ገብርኤል ለማክበር በመጓዝ ላይ የነበሩ ናቸው።

No comments:

Post a Comment

wanted officials