Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, December 27, 2016

ሕወሓት የአርበኛ ጎቤ መልኬ ቤተሰቦች ጋር የሚያሸማግሉትን ላከ


የጎንደር ሕብረት ዘጋቢ ዞብል ከጎንደር እንደዘገበው በአሁኑ ወቅት የሕወሓትን ሰራዊት እየተፋለመው የሚገኘው አርበኛ ጎቤ መልኬ ቤተሰቦች ጋር ሕወሓት አማላጅ በመላክ አስታርቁኝ አለ:: እንደ ዘጋቢው ገለጻ ከሆነ ከቤተሰቡ በኩል የተገኘው ምላሽ አያገባንም የሚል ነው::

ዞብል በዘገባው አርበኛ ጎቤ ሕወሃት የወልቃይት የአማራ ማንነት እና የነጻነት ጥያቄ ባነሱ ዜጎች ላይ በወሰደው ግድያ፣ እስራት እና ድብደባ ተማረው ሕወሃትን እስከወዲያኛው ለማስወገድ ቆርጠው በመነሳት ዱር ቤቴ ካሉት አርበኞች (የነጻነት ታጋዮች) መካከል አንዱ ናቸው። ሕወሃት በአርበኛ ጎቤ የሚመራውን እና ሌሎችም የነጻነት ሃይሎች እያደረጉ ያሉትን የአርበኝነት ተጋድሎ በእንጭጩ ለመቅጨት ሳያሰልስ ወደ ስፍራው ጦሩን እያሰማራ ባለበት ሁኔታ ነው እንደወትሮው ሁሉ የአርበኛ ጎቤን ቤተሰቦች በማስገደድ፣ በማስፈራራት እና በመለማመጥ “ከአርበኛ ጎቤ ጋር ሸምግሉኝ” በማለት ላይ የሚገኘው። እንደ ዞብል ዘገባ ከሆነ የአርበኛ ጎቤ ቤተሰቦች ለሕወሃት “አስታርቁኝ” ጎትጎታ የሰጡት ምላሽ፣ “…ስለ ጎቤ እኛ ሽምግልና መቀመጥ አንችልም እራሱን ወደአለበት ቦታ ሒዳችሁ እንደፈለጋችሁ አድርጉት” የሚል ነው።
ሃብትና ንብረቱን ጥሎ በረሃ በመግባት እየታገለ የሚገኘው አርበኛ ጎቤ መልኬና የሚመራው ጦር የኢትዮጵያን ሕዝብ ድጋፍ እንደሚፈልግ መግለጹ የሚታወስ ነው::
ይሁንና ሕወሃቶች ተስፋ ባለመቁረጥ የአርበኛ ጎቤ ቤተዘመዶችን ሁሉ እያፈላለጉ “ሂዱና ከመንግስት ጋር አሸማግሉት” በማለት ላይ ይገኛሉ። ሕወሃት ከዚህ ቀደም ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱን ጨምሮ በርካታ ነጻነታቸውን ለመቀናጀት ዱር ቤቴ ያሉ አርበኞችን በሽምግልና ስም ከመለሰ በኋላ ለእስርና ሞት እንደሚዳርጋቸው ይታወቃል።

No comments:

Post a Comment

wanted officials