Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Monday, December 12, 2016

የሕወሓት መንግስት የአማራ አንድ ከፍተኛ ባለስልጣንን ከስልጣን አንስቶ የቁም እስረኛ አደረገ

 በአማራ ክልል በተለይም በጎንደር እና በጎጃም እየተደረገ ያለው ሕዝባዊ አመጽ በተቀጣጠለበት በዚህ ወቅት የትግራዩ ነጻ አውጪ መንግስት የክልሉን ጸጥታና አስተዳደራዊ ዘርፍ ዋና ኃላፊን ከስልጣን አንስቶ አባረራቸው::
እንደ ምንጮች ገለጻ ከሆነ ለሕወሓት መንግስት ታማኝ ናቸው ተብለው በተደጋጋሚ ይነገርላቸው የነበሩት አቶ ደሴ ዓለሜ በአማራ ክልል ከተነሳው ሕዝባዊ አመጽ ጋር በተያያዘ ስልጣናቸውን አጥተዋል::
በአሁኑ ወቅት ካለምንም ሥራ ቤት ቁጭ ብለው የሚገኙት አቶ ደሴ ዓለሜ በቁም እስር ላይ እንደሆኑም ምንጮቻችን ዘግበዋል::
የሕወሓት መንግስት የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸውን በተደጋጋሚ ከልጣናቸው ለማንሳት ሞክሮ የነበረ ቢሆን ሕዝብ ይነሳብኛል በሚል ሃሳቡን ሲቀያይር ቆይቷል:: በተለይም አቶ ገዱን የአርበኞች ግንቦት 7 ተላላኪ ነው እያሉ የሕወሓት ሚዲያዎች በአደባባይ እስከመተቸት የደረሱበት ሁኔታ ተስተውሏል::

No comments:

Post a Comment

wanted officials