Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Monday, August 24, 2015

ለ36ኛ ግዜ የዞን9 ጦማርያን የፍርድ ቤት ውሎ ቀጠሮ ለጳጉሜ 2 /2007 ተቀጠረ።

በነሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ ለመከላከል ወይም ሳይከላከሉ በነፃ ለመሰናበት ውሳኔ ዛሬ ለ35ተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበው የነበሩት አራቱ በእስር የሚገኙት ጦማርያን በድጋሚ በተለዋጭ ቀጠሮ ተሸኝተዋል።
በዛሬው ውሎ ችሎቱ ያልተሰየመ ሲሆን ተከሳሾች እና ጠበቆች በቢሮ ተጠርተው ዳኞች ተሟልተው ስላልተገኙ ችሎቱ ለመሰየም አለመቻሉን ዶክመንቶችን ማየትና ውሳኔውን ፅፎ ማጠናቀቅ አሁንም እንዳልቻሉ በመግለፅ ዳኛ ዘሪሁን ለጷግሜ 2 ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠታቸውን አሳውቀዋል።
መደበኛ የወንጀል ችሎት ከነሃሴ 15 ጀምሮ የተዘጋ ሲሆን የዞን9 ጦማርያን ከመዘጋቱ በኃላ በሁለተኛ ልዮ ቀጠሮ እና በአጠቃላይ 36ተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ተመልሰው ይቀርባሉ ።

No comments:

Post a Comment

wanted officials