Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, March 29, 2016

ከጎንደር ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኘው አይምባ በተባለ አካባቢ ትናንት በደረሰ የተሸከርካሪ አደጋ የ10 ሰዎች ህይወት አለፈ


ከጎንደር ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኘው አይምባ በተባለ አካባቢ ትናንት በደረሰ የተሸከርካሪ አደጋ 10 ሰዎች ሞተዋል::
አደጋው የደረሰው ልዩ ስሙ አዘዞ ሎዛ ማርያም አይነኩራ በተባለ አካባቢ፥ ከተቃራኒ አቅጣጫ ይጓዙ የነበሩ ሁለት ሚኒባሶች እርስ በእርስ በመጋጨታቸው ነው፡፡
154039451_676b7268e6_b
ትናንት 7 ሰዓት ከ30 ላይ በደረሰው የትራፊክ አደጋ 10 ሰዎች ሲሞቱ በ22 ተሳፋሪዎች ላይ ደግሞ ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሷል፡፡
በአደጋው የሁለቱም ተሽከርካሪዎች ሾፌሮች ህይዎት አልፉአል::
ጉዳት የደረሰባቸው መንገደኞችም በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል።
የአደጋው መንስኤ ሁለቱ ተሽከርካሪዎቹ እርስ በእርስ ቦታ በመዘጋጋት የፈጠሩት የፊት ለፊት ግጭት መሆኑም ታውቛል::
ከአይምባ ወደ ጎንደር ይጓዝ የነበረው ኮድ 3 ሚኒባስ ትርፍ አሳፍሮ እንደነበር ጠቅሰው፥ ከጎንደር አይምባ ይጓዝ የነበረው ኮድ 2 ሚኒባስ ደግሞ አምስት ተሳፋሪዎች በውስጡ ነበሩ፡፡

No comments:

Post a Comment

wanted officials