Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, March 31, 2016

ወልቃይትና ጠገዴ በአጼ ዮሓንስ ዘመንም ትግራይ ውስጥ አልነበሩም ( የሰነድ ማስረጃው ይሄው) Abraham


***************************************************************
ከዚህ በላይ በጻፍኩት ሐተታ በ18ኛው ክፍለ ዘመን በ አጼ ቴዎድሮስ ዘመን ወልቃይትና ጠገዴ በትግራይ ስር እንዳልነበሩና : ይተዳደሩ የነበሩት በጎንደር በጌምድር ስር መሆኑን በመረጃ አይተናል:: ደሚቀጥለው ከመሻገራችን በፊት ለህሊናዎ ይሄንኑ በ18ኛው ክፍለ ዘመን የተጻፈ መረጃ ይመልከቱ
( http://library.si.edu/digital-libra…/…/routesabyssinia00cook)
እዚህ ሊንክ ላይ ቢጫኑ መጽሓፉን በነጻ ያገኙታል( ጽሁፉን በጉልህ ለማንበብ Control + ይጫኑ) :: ከገጽ 188 ጀምሮ በማያሻማ ሁኔታ እንደተጻፈው ዋልድባ : ወልቃይት ጠገዴ በቀድሞው በጌምድር ባሁኑ ጎንደር ስር እንደነበሩና የትግራይ ግዛት እንዳልነበሩ ነው::
አሁን ከአጼ ቴዎድሮስ ዘመን ወደ አጼ ዮሐንስ ዘመን እንጓዝና ወልቃይትና ጠገደ በማን ስር እንደነበሩ እንይ:: በተልይም አሁን ያሉ የትግራይ ብሔርተኞች የሚያነሱት ክርክር
” ወልቃይትና ጠገዴ እንዲሁም የሰሜን ወሎ ግዛቶች :በአጼ ዮሃንስ ዘመን በትግራይ ስር ነበሩ” የሚል ነው::
የኣጼ ዩሓንስ የልጅ ልጅ የሆኑት ራስ መንገሻ ሥዮም በግልጽ ይህ ትክክል አለመሆኑን : የትግራይ ድንበር ተከዜ እንደሆነና ተከዜን ተሻግሮ ያለው ወልቃይት የትግራይ አካል እንዳልነበረ ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል::
በአጼ ዮሐንስ ዘመን ኢትዮጵያ መጥቶ ኢትዮጵያን ካርታ አንስቶ የሄደው ፈረንሳዊው የካርታ ባለሙያና የዓለሙ የካርታ ድርጅት በ18ኛው ክፍለ ዘመን ያሳተመውም መጽሓፍ የሚያረጋጝጠው ይሄንኑ ነው:: Elis Reclus የተባለው ፈረንሳዊ የካርታ ስራ ና የጂኦግራፊ ባለሙያ The Earth and its Inhabitants : North East Africa በሚለው መጽሃፉ ወልቃይት : ጠገዴ ና ጠገዴ ን በስም እየጠቀሰ የበጌምድር ግዛቶች ( ያሁኑ ጎንደር) እንጂ የትግራይ ግዛቶች እንዳልነበሩ በማያሻማ መልኩ ጽፎታል:: ይህ የካርታ ባለሙያ መጽሓፉን ያሳተመው በኣጼ ዮሓንስ ዘመን ነው:: ኢትዮጵያ ድረስ መጥቶ አጼ ዮሐንስና መኳንቶቻቸውን አናግሮ : ኢትዮጵያን ዞሮና ተመራምሮ ያገኘው የወቅቱን እውነት ነው ያሰፈረው:: መጽሓፉን ለማግኘት ይሄንን ሊንክ ተጭነው ገጽ443 ያንብቡ::
https://play.google.com/store/books/details?id=Y4WbCSAU7kQC
ምናልባት ጎግል አካውንት ከሌላችሁ ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ በመጫን መጽሃፉን ማውረድ ይቻላል:: ይህ መጽሓፍ ከተጻፈ ከመቶ ዓመት በላይ ስለሆነው በማይክሮ ፊልም አርካይቭ ውስጥ ገብቷል:: ለማንበብ ካስቸገሮ ኮንትሮል ፕላስ እየተጫኑ ከገጽ 443 ጀምሮ ያለውን ያንብቡ
https://archive.org/stream/cihm_40198#page/n568/mode/1up
ይህም ካልተቻለ ከዢህ ጽሁፍ በታች ( ኮሜንት ላይ) ገጹን ስለለጠፍኩት ማየት ይቻላል::
እነ ዶክተር ገላውዴዎስ ” ወልቃይት ከጥንት ጀምሮ በትግራይ ስር አልነበረችም የሚለው ያታሪክ መሰረት የለውም :: ስህተት ነው:: … እነዚህ ሰዎች ከጀርባቸው ሌላ አካል አለ:: ” በማለት ያለተጻፈ የሚያነቡት ከየት አምጥተው ይሆን? ዘረኝነት ይሄን ያህል ሰውን ያሳውራል?
ይቀጥላል

Netsanet Beqalu's photo.

No comments:

Post a Comment

wanted officials