Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, March 31, 2016

ኢሳት ዜና-------ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም አምባሳደሮችን እየተማጻኑ ነው


tewedrosየህወሃቱ አመራር አባልና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሀኖም ለተመድ የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተርነት ቦታ ለመወዳደር የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችን መንግስታቸውን አሳምነው ድጋፍ እንዲሰጡ ያደርጉላቸው ዘንድ በመማጸን ላይ መሆናቸው ታውቁዋል።
ሰሞኑን በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተቀማጭነታቸው በአዲስ አበባ የሆኑ የአፍሪካና የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራትን አምባሳደሮች መንግስቶቻቸው በምርጫው ድጋፋቸው እንዲሰጡዋቸው ያደርጉላቸው ዘንድ ሲማጸኑ ተሰመቱዋል። አምባሳደሮቹም በዲፕሎማሲ አነጋገር የተቻላቸውን እንደሚያደርጉ ገልጽውላቸዋል።
ዶ/ር ቴዎድሮስ በአሁኑ ወቅት መደበኛ ስራቸውን በመተው በመንግስት በጀት በምረጡኝ ቅስቀሳ የኤምባሲዎችን ደጅ እየጠኑ ሲሆነ፣ ዶ/ሩ እኔ ብመረጥ አፍሪካም ጭምር ትጠቀማለች በሚል የቅስቀሳ ዘዴ ድጋፍ እየጠየቁ ሲሆኑ የአለም ጤና ጥበቃ ድርጅት የዳይሬክተርነት ቦታ በተለይ እንደአሜሪካና እንግሊዝ ያሉ የሀያላን ሀገራት ደጋፍ ማግኘት ካልቻሉ በስተቀር የማለፋቸው ነገር አጠራጣሪ ነው።
በአሁኑ ወቅት የጤና ድርጅቱን በዋና ዳይሬክተርነት እየመሩ ያሉት ዶ/ር ማርጋሬት ቻን በሀገራቸው ሆንግኮንግ የጤና ሚኒስትር ሆነው ከመስራታቸውም በላይ በአለም የጤና ድርጅትና በሌሎችም አለም አቀፍ ድርጅቶች በከፍተኛ ሀላፊነት የሰሩ መሆናቸው ሲመዘን፣ በብቃትም ጭምር ዶ/ር ቴዎድሮስ ለቦታው እንደማይመጥኑ ከወዲሁ አስተያየት እየተሰጠባቸው ነው። ዶ/ሩ በኢትዮጵያ ባለፉት 24 አመታት ለተፈጸሙት የሰባዊ መብት ጥሰት ተጠያቂ ናቸው በሚል፣ እርሳቸው እንዳይመረጡ በማህበራዊ ሚዲያ ቅስቅሳ ሲደረግ ቆይቶአል።
ዶ/ር ማርጋሬት እ ኤ አ ጁን 30/2017 ሀላፊነታቸው ስለሚያበቃ የአለም ጤና ጥበቃ ድርጅቱ ጠቅላላ ጉባኤ ተሰብስቦ በእሳቸው ምትክ አዲስ ዳይሬክተር አወዳድሮ ይሾማል ተብሎ ይጠበቃል።

ኢሳት ዜና

No comments:

Post a Comment

wanted officials