Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Friday, March 25, 2016

«የዶክተር» ገላውዲዮስ አርኣያ አይን ያወጣ ውሸት!

«የዶክተር» ገላውዲዮስ አርኣያ አይን ያወጣ ውሸት!
ኒዮርክ ውስጥ «ታሪክ» የሚያስተምሩት የትግራይ ብሔርተኛው «የታሪክ ዶክተር» ገላውዲዮስ አርኣያ፤ ትናንትና በአሜሪካ ድምጽ ትግርኛ ክልፍ ቀርበው «በታሪክ ወልቃይት የትግራይ እንደነበር» ሲያስረዱ በ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በElizabel Filleul በፖርቹጋል ቋንቋ የተጻፈውን «Tractatus tres historico-geographici (1634): A seventeenth century historical and geographical account of Tigray, Ethiopia (Aethiopistische Forschungen)» መጽሀፍ ጠቅሰው ነበር። ይህ መጽሀፍ ወደ እንግሊዝኛ ተተርጉሟል።
እስቲ ዶክተር ገላውዲዮስ አርኣያ የጠቀሱት የElizabel Filleulን መጽሀፍ ስለ 17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የትግራይ ግዛት ምን ይነግረናል? ዶክተር ገላውዲዮስ አርኣያ በጠቀሱት መጽሀፍ የመጀመሪያ ምዕራፍ የመጀመሪያ ገጽ ላይ ስለትግራይ ግዛት [ ከሰሜን እስከ ደቡብ፤ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ] እንዲህ ተጽፎ እናገኛለን፤
<<Among all the kingdoms that the Emperor of Ethiopia possesses today one of the greatest if not the greatest and the most important is the kingdom Tigre. From north to south, that is from the limits of the Hamasen to Enderta, it covers an areas of from ninety to one hundred leagues (3.2 miles); and from the east, which is besides Dancali, located at the entrance to the Red sea to the southern end of the Red Sea, to the west bounded by the Tekezze River beside the Semen, it covers an area of similar size, so that the Kingdom has a nearly circular shape. >>
ይህ በመጽሀፉ የመጀመሪያ ገጽ ላይ የሰፈረ ጥሬ ሀቅ ነው። መጽሀፉ ውስጥ ይህ ሀቅ ተቀምጦ ሳለ ዘረኛው ዶክተር ገላውዲዮስ አርኣያ ግን ትግርኛ ማንም አይሰማም ብለውና መጽሀፉን ፈልጎ የሚያጋልጠኝ ሰው አይኖርም በሚል መጽሀፉ ላይ ያልተጠቀሰ ታሪክ በቃለ መጠይቃቸው ወቅት በማቅረብ ክህደት ፈጽመው አጭበርብረዋል። በነገራችን ላይ ይህ የዶክተር ገላውዲዮስ አርኣያ ማጭበርበር በacademic crime የሚያስቀጣ ትልቅ ወንጀል ነው። ቀስፎ የያዛቸው የአማራ ጥላቻ እድሜ ልካቸውን ከኖሩበት ሞያቸው ጋር አፋትቶ academic crime አሰርቷቸዋል።
ዶክተር ገላውዲዮስ አርኣያ የተዋረዱት በምሁርነት ካባ የወያኔ ፕሮጀክት ለሆነው አማራን የማጥፋት ፕሮግራም በግብረ አበርነት ለማገዝ ባደረጉት የክህደት ምስክርነታቸው ነው። እኒህ ሆዳም ምሁር የታሪክ እውቀታቸውንና ሽማግሌነታቸውን በቅሌት መንዝረው ከታሪክ «ምሁርነት» ወደ ትንሽ ካድሬነት የወረዱ ተራ ዋሾ ናቸው።
አንድ የታሪክ «ዶክተር ነኝ» የሚል ግለሰብ ማንም ተራ አንባቢ ሊያረጋግጠው የሚችለውን የታሪክ እውነት ባደባባይ በማዛባት የታሪክ ሀቅን ለዘረኝነት ጥማቱ ማርኪያ እየጠመዘመ በማበላሸት የሚያቀርበው ከሆነ፤ ሌላው «በሞያው» የሚጽፈው «የታሪክ ጭብጥ» እንዴት ሊታመንለት ይችላል?
እንግዲህ ዶክተር ገላውዲዮስ አርኣያ በአደባባይ የሚዋሹ ተራ ግለሰብና በዘረኝነት የታጠቡ ውሸታም አስተማሪ እንጂ የታሪክ ምሁር እንዳልሆኑ ማንም ሊያውቅ ይገባል። የምሁርነትን ዋነኛ ባህሪ ማለትም integrityን የማያሟሉትን እኒህን ተራ ዋሾ ግለሰብ ኒዮርክ ውስጥ ለሚያስተምሩበት የታሪክ ትምህርት ክፍል በስልክና በኢሜል ይህንን ጉዳቸውን ሪፖርት በማድረግ ማጋለጥ አለብን። እንደዚህ አይነቱ ዘረኛና ለራሱ ክብር የሌለው ተራ ሸበቶ ግለሰብ «የኢትዮጵያን ታሪክ አጥኚ» ተብሎ በስማችን ሊጠራ አይገባም።
ዶክተር ገላውዲዮስ አርኣያ በቪኦኤ ላይ ቅርጥፍ አድርገው የዋሹበት ቃለ መጠይቃቸው እነሆ፤
http://m.tigrigna.voanews.com/a/welkite-tseged…/3253236.html
ዶክተር ገላውዲዮስ አርኣያ የተዋረዱበት የElizabel Filleul መጽሀፍ፡ «Tractatus tres historico-geographici (1634): A seventeenth century historical and geographical account of Tigray, Ethiopia (Aethiopistische Forschungen)» ውስጥ ስለ ትግራይ ግዛት የተጠቀሰውንና ከፍ ብዬ ያቀረብሁትን የታሪክ እውነት ከመጽሀፉ ገጽ ሁለት ፎቶ አንስቼ ከታች በድጋሜ ለጥፌዋለሁ።

No comments:

Post a Comment

wanted officials