Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Friday, March 4, 2016

23 ዓመቷን ኩዌታዊ ገድላ ራሷን አቆሰለች የተባለችው ኢትዮጵያዊት ማምሻውን አረፈች

ነቢዩ ሲራክ 
በኩዌት “ኢትዮጵያዊቷ የቤት ሰራተኛ የ23 ዓመቷን ፋጢማ የተባለችን ኩዌታዊ የአሰሪዋን ልጅ ገድላና ራሷን አቁስላለች ” በሚል በፖሊስ ጥበቃ ላለፉት ሳምንታት ሳባ በሚባል ሆስፒታል ህክምና ላይ የነበረችው ኢትዮጵያዊት ዛሬ ሐሙስ ከምሽቱ አራት ሰዓት አካበቢ ማረፏን አረጋግጫለሁ ። ሆስፒታል ከገባች ጀምሮ በኩዌት ኤንባሲ ስትጠየቅ የሰነበተችው እህት ከቀናት በፊት በተሻለ ጤንነት ላይ እንደነበረች ተጠቁሟል ። በአካል ያዩዋት ወገኖች በተለይ በአንገቷ ላይ ተተክሎ የነበረው ቱቦ ተነስቶላት እንደነበርና ለመናገር ሙከራ ታደርግ እንደ ነበር አጫውተውኛል ።
በተመሳሳይ ሁኔታ ከሳምንት በፊት የተለቀቁት መረጃዎች ይህችው እህት ከጉዳቷ እንዳገገመች ተነግሮ ነበር ። ይሁን እንጅ የዛሬ ምሽት ” አሟሟቷ ከልብ ህመም ጋር በተገናኘ ነው ” የሚል መልስ በሆስፒታሉ እየተሰጠ እንደሆነ ጉዳዩን የሚከታተሉት ወገኖች መረጃውን አጋርተውኛል ! አንዳንድ መረጃውን የሰሙ ወገኖች በበኩላቸው ” በግድያው ወቅት ያን ያህል ደሟን ፈሷ ልቧ ሰከክ ሳይል እንዴት በልብ ህመም ህይዎቷ አለፈ ይባል ? ” በማለት ያጠይቃሉ!
ነፍስ ይማር !Kuwait
ነቢዩ ሲራክ
የካቲት 25 ቀን 2008 ዓም

No comments:

Post a Comment

wanted officials