Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, March 31, 2016

ሕወሓቶች ገዱ አንዳርጋቸውን አንገቱን ለማስደፋት ዘምተዋል | “ግንቦት 7 ነው… የአንዳርጋቸውን ራዕይ እያስፈጸመ ነው” እያሉ እየወነጀሉት ነው

ሕወሓቶች ገዱ አንዳርጋቸውን አንገቱን ለማስደፋት ዘምተዋል | “ግንቦት 7 ነው… የአንዳርጋቸውን ራዕይ እያስፈጸመ ነው” እያሉ እየወነጀሉት ነው

የብአዴን ምክትል ሊቀመንበርና የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸውየብአዴን ምክትል ሊቀመንበርና የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው
ወልቃይትን ጨምሮ በአማራ ክልል እየተነሱ ያሉትን የመብት ጥያቄዎች ተከትሎ ሕወሓቶች “ገዱ አማራውን በትግራይ ሕዝብ ላይ እያስነሳው ነው” የሚሉ ዘመቻዎችን መክፈታቸው ታወቀ:: ይህም ዘመቻዎች የአማራ ክልል ር ዕሰ መስተዳደርን አንገት ለማስደፋት የታቀደ ሲሆን ዘመቻው በድርጅቱ ውስጥ ብቻ ሳይሆን በሶሻል ሚድያዎችም ጭምር ተጀምሯል:: ከሕወሓቱ አባይ ወልዱ ጽህፈት ቤት በወጣ ትዕዛዝ የወልቃይትን እና ሌሎች የአማራ ሕዝብን ጥያቄ ተከትሎ በገዱ አንዳርጋቸው ላይ እየተሠራጩ ካሉት ጽሁፎች መካከል አንዱ የሚከተለው ነው:: ለግንዛቤ ይረዳ ዘንድ ያንብቡት::
የገዱ ነገር፤
—————————-
-ገዱን ሳስበው በገዱ አንዳርጋው ፅጌ መታሰር ውስጡ ብግን እርር ድብን ያለ ዓይነት ሰው ይመስለኛል፡፡
የገዱን የባለፉት ሁለት ዓመታት ድርጊቶች መለስ ብሎ ላስታወሰ፤
-አንደኛ፤ የምዕራብ ትግራይ አካበቢዎችን የሃሰት አማራ ማንነት ኮሚቴ በስውር አደራጅቶና ረድቶ ለፌደሬሽን ም/ቤት አብቅቶዋል፡፡
-ሁለተኛ፤የቅማንትን ህዝብ መብት ለማፈን ባደረገው ጥረት ህዝብን በወታደሮቹ እስከማስጨፍጨፍ ደርሶዋል፡፡
-ሶስተኛ፤ በአሁኑ ግዜ ደግሞ በትግራይ ተመርተው በትግራይ ልጆች በአመራ ክልል የሚከፋፈሉ ምርቶች ላይ የተለያዪ ችግሮች በመፍጠር ላይ ነው፡፡
-አራተኛ በክልሉ የሚገኙ አንዳንድ አካባቢዎች መጠርያዎችን በክልሉ ም/ቤት እያስፀደቀ በማስቀየር ላይ ነው፡፡ ለምሳሌ መተማ ዪሃንስን ወደ መተማ…በአማራ ክልል ያለውን የፀገዴ ክፍልን ወደ ጠገዴ፣ፀለምቲን ወደ ጨለምት አንዳንዴ ደግሞ ወደ ጠለምት ወዘተ፡፡
በተለይ ከላይ ከተገለጡት ውስጥ እጅግ በጣም አሳሳቢዊ ጉዳይ ደግሞ ገዱ በሚመራው ክልል በተለይ በአርማጭሆና ሌሎች አካባቢዎች የግንቦት ሰባት ሃይሎች እንደፈለጉ የሚፈነጩበት በተለይ በአካባቢው የትግራይ ነዋሪዎች ላይ የተለያዪ ጥቃቶችን የሚፈፅሙበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡
ይህ ነገር በትልቁ አንድ ነገር እንድናስታውስ ያስገድደናል፤ ይሀውም የአሸባሪው ግንቦት 7 መሪ ብርሃኑ ነጋ ትግላችን ወደ አገር ውስጥ ገብቶዋል ያሉበትን አጋጣሚ፡፡
እንግዲህ የብርሃኑ ነጋን አነጋገር ልብ ላለው ሰው የገዱ ክልሉን ያለመጠበቅ ጉዳይን ለምን ብሎ መጠየቅ አለበት፡፡
በበኩሌ አንዳርጋቸው ፅጌ የታሰረው በአካል እንጂ በዓላማና በመንፈስ ግን እነ ገዱ በእልህ ራዕዪን እያስቀጠሉ ያሉበት ሁኔታ በተግባር እያየን ነው፡፡
እስኪ ራሳችሁን ጠይቁ፤ አንዳርጋቸው ፅጌ ባይታሰር ኑሮ አሁን በአማራ ክልል ከምናየው ሁኔታ የተለየ ምን ይፈጥር ነበር! መልሱ ምንም ነው፡፡ ግንቦት በአማራ ክልል ምዕራባዊና ሰሜናዊ አከባቢዎች ሽፍቶችን አሰማርቶ የሰላማዊ የሰዎችን ሰላምና ልማት ማወክ የጀመረው በምን ምክንያት ነው፡፡
እንግዲህ ኢህአዴግ ውስጡን ማየት ያለበት እንዚህ ከላይ የተገለጡት ሌሎችንም ክስተቶች በማገናዘብ መሆን አለበት፡፡
በበኩሌ የግንቦት 7 ትግል የገባው አማራ ክልል ብቻ አይደለም ቤተ-መንግስት ጭምር እንጂ!
ኢህአዴግ ውስጡን ከትምክህተኞችና የምኒሊክ ዙፋን አስመላሾች ያፅዳ!
(አንዳርጋቸው ጽጌስ ከዚህ በላይ ምን ያደርግ ነበር…..ምንም!)

No comments:

Post a Comment

wanted officials