Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Thursday, March 31, 2016

ጎንደር ለሪፈር አንልክም የተባለች የወልቃይት ነዋሪ ህይወታ ማለፉ ተነገረ

ጎንደር ለሪፈር አንልክም የተባለች የወልቃይት ነዋሪ ህይወታ ማለፉ ተነገረ

የወልቃይት ነዋሪ የሆነችው የ30 ዓመቷ ወላድ እናት በኹመራ ሆስፒታል በ19/07/08 የቀዶ ጥገና ህክምና ተደርጎላት በሰላም ከተገላገለች በኋላ ተጨማሪ ህክምና የሚያስፈልጋት በመሆኑ የሆስፒታሉ ሐኪሞች የተሻለ ህክምና እንድታገኝ ወደ መቀሌ እንድትሄድ ሪፈር ሊጽፉላት ይዘጋጃሉ፡፡
በኹመራ ሆስፒታል የነበሩ የእንኩየውሽ ገሌ ቤተሰቦች ወደ መቀሌ ሳይሆን ወደ ጎንደር ሆስፒታል መውሰድ እንደሚፈልጉ በመግለጽ ዶክተሮቹን ለጎንደር ሆስፒታል ይጽፉላቸው ዘንድ ይማጸናሉ፡፡ነገር ግን የካህሳይ አበራ ሆስፒታል ዶክተሮች የተጠየቁትን ለማድረግ ፈቃደኛ ሳይሆኑ ሶስት ቀናትን ‹‹ለጎንደር ሆስፒታል አንጽፍም ››በማለት ያባክናሉ፡፡
ከሶስት ቀናት ጭካኔ በኋላ ህመምተኛዋ እየተዳከመች መምጣቷን የተመለከቱት ዶክተሮች ለጎንደር ሆስፒታል ሪፈር ይጽፋሉ፡፡እንኩየውሽ ጎንደር ሆስፒታል በደረሰች በሁለት ሰዓታት ልዩነት ውስጥም ህይወቷ በማለፉ ይህችን አለም ተሰናብታለች፡፡

No comments:

Post a Comment

wanted officials