Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Monday, March 28, 2016

የሰማያዊ ፓርቲ ዲሲፕሊን ኮሚቴ ሊቀመንበሩን ኢንጂነር ይልቃልን እና አቶ ወረታውን አባረርኩ አለ

የሰማያዊ ፓርቲ ዲሲፕሊን ኮሚቴ ሊቀመንበሩን ኢንጂነር ይልቃልን እና አቶ ወረታውን አባረርኩ አለ

(ምንሊክ ሳልሳዊ) – ጠንካራ ፓርቲዎችን ሰርጎ ገብ አስገብቶ በመበታተን ጠንካራ አመራሮችን በመወንጀል ፓርቲዎችን አዳክሞ ብመቃብራቸው ላይ ተለጣፊ ታማኝ ተቃዋሚዎችን የሚተክለው ኢሕኣዴግ በሰማያዊ ፓርቲ ውስጥ ገብቶ እየበጠበጠ እንደሚገኝ ከተለያዩ ምንጮች የሚወጡ ዘገባዎችን ተመልክተናል::

ፓርቲውን ለመቆጣጠር ፍላጎት ያለው ኢሕኣዴግ በሚደጉባቸው ሪፖርተር እና አዲስ አድማስ ጋዜጦች በኩል የፓርቲ አመራሮችን ስም ካለማስረጃ እና የፍትህ ውሳኔ ሲያጠፉ ከርመዋል::
በዛሬው እለት የተሰማው ዜና ደግሞ የሰማያዊ ፓርቲ ልሳን የነገረ ኢትዮጵያ አዘጋጅ በትዊተር ገጹ በዚህ መሰረት የድርጅቱ ሊቀመንበር ይልቃል ጌትነት እና ወረታው ዋሴ ከፓርቲው ሲባረሩ ወይንሸት ሞላ እና ስለሺ ፈይሳ ለ2 አምት ከማነኛውም የአመራርነት ቦታ ታግደዋል።ሰማያዊፓርቲ ሊቀመንበሩንና የቀድሞው የፋይናንስ ኃላፊን ከፓርቲው አባረረ። ሆኖም የሊቀመንበሩ መባረር ተግባራዊ የሚሆነው ከጠቅላላ ጉባኤ በኁዋላ መሆኑን እርምጃውን የወሰድው የዲስፕሊን ኮሚቴ ገልጹዋል ሲል ጽፏል::
Yilikal Getenet

No comments:

Post a Comment

wanted officials