Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Friday, February 26, 2016

የጅማ ህዝብ ተነሳ – በቀለም ወለጋ ሕዝብ በጩኸት አጋዚ በጥይት እየታገሉ ነው * 4 ሰልፈኞች ተሰውተዋል




(ዘ-ሐበሻ) የሕወሓት መንግስት ጠቅላይ ሚኒስተር ኃይለማርያም ደሳለኝ ዛሬ የመንግስት ጋዜጠኞችን ሰብሰበው በኦሮሚያ ክልል ሰልፍ የወጡ ነጹሃንን ካላረፉ የማያዳግም እርምጃ እንወስዳለን ሲሉ ቢያስፈራሩም በኦሮሚያ ክልል ግን ይህን የርሳቸውን ቃል የሚሰማ እንደሌለ በየከተማው እየተደረጉ ያሉ ተቃውሞዎች አሳይተዋል::
Jima
በቀለም ወለጋ በጊዳሚ ወረዳ በቡሪ መንደር ዛሬ በተደረገ ከፍተኛ ተቃውሞ የአጋዚ ጦር በሕዝቡ ላይ ጥይት አንዝንቦ ከ40 በላይ ሰዎችን ሲያቆስል 4 ሰዎችን እንደገደለ ለዘ-ሐበሻ የመጡ መረጃዎች አሳይተዋል:: ሕዝቡ በሰላማዊ መንገድ ጥያቄው እንዲመለስ መንግስትም እንዲለቅ እየጠየቀ ባለበት ወቅት በተለይም ከቤንሻንጉል እና ከጋምቤላ አካባቢ የመጡ የአጋዚ ጦር አባላትይ ሕዝቡ ላይ ተኩሰዋል:: እነዚህ የቤንሻንጉል እና የጋምቤላ የአጋዚ ጦር አባላት አማርኛም ሆነ ኦሮሚኛ የማይነገሩ በመሆኑ የኦሮሞ ሕዝብ ምን እያለ እንደሚጮህ እንኳ የሚረዱ አይደሉም የሚሉ በስፍራው ያሉ የዘ-ሐበሻ ምንጮች ሕወሓት መንግስት በምርጫ 97 ማግስት በሕዝብ ላይ የተለያዩ ቋንቋዎች የሚናገሩ ወታደሮችን ከሌላ ክልል በማስመጣት የፈጸመውን ተመሳሳይ ፍጅት በኦሮሚያም እየደገመው ነው ብለዋል::
የኦሮሞ ሕዝብ ተቃሞ በጉጂም በረካ ሕዝብ በአደባባይ ወጥትቶ ዛሬም ተቃውሞውን ሲያሰማ ነው የዋለውም:: በተለም በቀንቻ ከተማ ከህፅአነት እስከ አዋቂ ከፍተኛ ተቃውሞ ሲያሰማ የኦሮሚያ ፖሊስ ከሕዝብ ጋር በመሆን ያለውን አጋርነት አሳይቷል:: በተለይ በዛሬው ተቃውሞ የኦሮሚያ ፖሊስ የጉጂን ሕዝብ አጅቦ እንደነበርና ከጥቃትም ሲከላከል እንደነበር የዘ-ሐበሻ ምንጮች አስታውቀዋል::
tekawemo
በጅማ እስካሁን የኦሮሞ ህዝብ እንቅስቃሴ ከተጀመረ በኋላ አሳይቶት የነበረውን ዝምታ በመስበር ዛሬ በ ሻቤ ሶዶ ከተማ በዓይነቱ ልዩ የነበረ ት ዕይንተ ህዝብ ታይቷል:: በጅማ ከሕፃናት እስከ አዋቂ አደባባይ በመውጣት በስር ዓቱ ላይ ያለውን ጥላቻ ገልጾ የሕወሃት መንግስት አካባቢውን ለቆ እንዲወጣ ሲጠይቅ እንደነበር ምንጮቻችን አስታውቀዋል::
west welega
በሌላ በኩል በምስራቅ ወጋ ቆዶላ ከተማም እንዲሁ ሕዝቡ አደባባይ ነበር የዋለው:: እንደ ሪፖርቶች ገለጻ በምስራቅ ወለጋ በቆዳላ ከተማ በነበረው ተቃውሞ አጋዚ ሠራዊት ሕዝቡ ላይ እንዲሁ ሲተኩስ ነበር:: እነዚሁ ዱላ የያዙትና በዝማ

No comments:

Post a Comment

wanted officials