Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Sunday, February 21, 2016

በአምቦ እስር ቤት ተቃጠለ | ከተማዋ በጥይት ድምጽ ተወጥራለች

በአምቦ እስር ቤት ተቃጠለ | ከተማዋ በጥይት ድምጽ ተወጥራለች
በአምቦ ከፍተኛው ተቃውሞ በቀጠለበት በዚህ ወቅት በከተማዋ የሚገኘው እስር ቤት በ እሳት እየነደደ መሆኑን የዘ-ሐበሻ ምንጮች አስታወቁ::
በተለምዶው ቀበሌ 06 ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኘው ይኸው የፖለቲካ እስረኞች ማሰቃያ እስር ቤት ውስጥ ከኦሮሞ ሕዝብ ንቅናቄ ጋር በተያያዘ የታሰሩ በርካታ ወገኖች እንደደሚገኙበት ምንጮች አስታወቀዋል::
በአምቦ ከተማ በአሁኑ ወቅት የጥይት እሩምታ እየተሰማ ሲሆን ከዚህ እስር ቤት እስረኞች ያምልጡ አያምልጡ ዘ-ሐበሻ እያጣራች ትገኛለች:: ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስም በ እስረኞች ላይ ከባድ ጉዳት ስለመድረሱ የታወቀ ነገር የለም::

No comments:

Post a Comment

wanted officials