Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Monday, February 29, 2016

አርበኞች ግንቦት በበርን ስዊዘርላንድ የተሳካ ህዝባዊ ውይይት አደረገ

አርበኞች ግንቦት በበርን ስዊዘርላንድ የተሳካ ህዝባዊ ውይይት አደረገ

የካቲት ፳፩ (ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የንቅናቄው አመራር የሆኑት አርበኛ ኤፍሬም ማዴቦ፣ ጋዜጠኛ አፈወርቅ አግደው ፣ የኢሳት ቴሌቪዥንና ሬዲዮ የጀርመን ሃገር ቃል አቀባይ ሃይሉ ማሞ፥ ተቀማጭነታቸው በስዊዘርላንድ የሆኑ የሃይማኖት አባቶችና ከተለያዩ የስዊዘርላንድ ከተሞችና ከሙኒክ ጀርመን ከተማ በመጡ ሃገርወዳድ ኢትዮጵያውያን በታደሙበት በዚህ ታላቅ ህዝባዊ ውይይት ላይ የወቅቱ የሃገራችን ፖለቲካዊና ማህበራዊ ሁኔታ፣ የአርበኞች ግንቦት 7 የትግል እንቅስቃሴ ፣ ላለፉት 4 ወራት በመላው የኦሮሚያ ከተሞች እየተካሄደ ስላለውና በመቶዎች ለሚቆጠሩ ሰላማዊ የኦሮሞ ተማሪዎች፣መምህራና ሰራተኞች ክቡር ህይወት መጥፋትን ስላስከተለው የህዝብ እምቢተኝነት ፣ ከሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ተቆርጦ ለሱዳን ሊሰጥ ስለታሰበውና ርዝመቱ ክ 1600 ኪሎሜትር በላይ ስለሆነው መሬት ፣ የነፃነት ታጋዩ አርበኛ አንዳርጋቸው ፅጌ ወቅታዊ ሁኔታና የሱን ፈለግ ስለመከተልና ሰለሌሎችም በርካታ ጉዳዮች ተነስተው ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
የእለቱን ረዘም ያለ መርሃ ግብር የሸፈነው ተሰብሳቢዎች ካለምንም ገደብ ለአርበኛ ኤፍሬም ማዴቦ የንቅናቄያቸውን የፖለቲካ አካሄድና ፕሮግራም በተመለከተና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ ለሚሰነዘሩ ጥያቄዎች መልስ የሰጡበት ነበር።
ተሰብሳቢው አቶ ኤፍሬም ማዴቦ ለሚሰነዘሩላቸው ጥያቄዎች በሙሉ ለሚሰጧቸው ማብራሪያዎችና ገለፃዎች እንዲሁም እራሳቸውም ከሌሎች የትግል ጓዶቻቸው ጋር በመሆን እየከፈሉት ላለው እልህ አስጨራሽ መስዋእትነት ያለውን አክብሮት ገልፆ፤ የሞቀ ቤታቸውን፣ ልጆቻቸውንና ቤተሰባቸውን ትተው በርሃ ለወረዱ የነፃነት ታጋዮች የአብረናችሁ ነን መልእክት እንዲያደርሱላቸውም ጠይቀዋል።
ማንኛውም የትግል እንቅስቃሴ ካለሴቶች ተሳትፎ እውን እንደማይሆን ሁሉ ፣ ላለፉት በርካታ አመታት በስዊዘርላንድ ውስጥ በሚካሄዱ ህዝባዊ ተሳትፎዎች ከፍተኛ አስተዋፅ ላደረጉ ሴቶች የዝግጅቱ መሪዎች ያዘጋጁላቸውን የምስክር ወረቀት ከአርበኛ ኤፍሬም ማዴቦ እጅ ተቀብለዋል።
በመጨረሻም ለነፃነት ታጋዩ አንዳርጋቸው ፅጌ 61ኛ አመት የልደት በአል የተዘጋጀውን ኬክ የትግል አጋራቸው አርበኛ ኤፍሬም ማዴቦና በስዊዘርላንድ ከ3 አስርት በላይ የሰብአዊ መብት ታጋይ በሆኑት ወይዘሮ መሰረት ሃይሌ በጋራ በመቁረስ ፥ በአቶ አንዳርጋቸው የተደረሰውን የአርበኞች ግንቦት 7 የትግል መዝሙር በመዘርመር ፥ እንዲሁም ለዝግጅቱ መሳካት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደረጉትን ወገኖች በማስመስገን ተፈጽሟል።


No comments:

Post a Comment

wanted officials