Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Wednesday, February 3, 2016

በሾላ ገበያ የእሳት አደጋ ተነስቶ ሱቆች ነደዱ

(ዘ-ሐበሻ) በአዲስ አበባ በተለምዶ ስሙ ሾላ ገበያ በሚባለው አካባቢ ዛሬ እኩለ ቀን አካባቢ በተነሳ ቃጠሎ ሱቆች መንደዳቸው ተሰማ:: እንደ ዘ-ሐበሻ የአዲስ አበባ ዘጋቢዎች ከሆነ በሾላ ገበያ ፍራሽ ተራ አካባቢ ሱቆች በቃጠሎው ነደዋል::
በተለይ ፍራሽ ተራ አካባቢ ያሉ አንዳንድ እሳቱን ሊያባብሱ የሚችሉ ነገሮች ለ እሳቱ መስፋፋት አስተዋጽኦ ቢያደርጉም የአካባቢው ነዋሪም እሳቱን ሊያባብሱ የሚችሉ አንዳንድ እቃዎች ሲያሸሽ እንደነበር ገልጸዋል:: የአዲስ አበባ እሳት አደጋ ሱቆች ከነደዱ በኋላ አደጋው እንዳይስፋፋ የማጥፋት ሥራ እንደሰራ የሚገልጹት የዓይን እማኞች በሰው እና በሕይወት ላይ ጉዳት ስለመድረሱ ማስረጃ እንዳላገኙ ለዘ-ሐበሻ ገልጸዋል::
በሾላ ገበያ ፍራሽ ተራ አካባቢ የተነሳው ቃጠሎ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ንብረቶችን ቢያወድምም ትክክለኛው ቁጥር ግን አልታወቀም::
የዚህ የእሳት ቃጠሎ መነሻ አልታወቀም:: ሆኖም ግን በስልጣን ላይ ያለው መንግስት አመራሮች ከዚህ ቀደም በተለያዩ ቦታዎች ሊያስነሳቸውና ለሌላ ሰው ቦታውን ሊሸጠው የሚፈልገውን ቦታ የ እሳት አደጋ በማስነሳት ወንጀል ሲወነጀሉ መቆየታቸው ይታወሳል::
shola

No comments:

Post a Comment

wanted officials