Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Tuesday, December 15, 2015

ሀሮማያ እና አወዳይ ከተማው በሕዝቡ ቁጥጥር ስር ውሏል | በሁለቱ ከተሞች 6 ሰዎች መሞታቸው ተዘገበ | ቪዲዮም ይዘናል





(ዘ-ሐበሻ) በሃሮማያ እና በአወዳይ ከተማ ዛሬ ቀጥሎ የዋለው የሕዝብ ቁጣ ከተማዋን መንገዶች እስከመዘጋጋት መድረሱ ተሰማ:: እንደ ዘ-ሐበሻ የዜና ምንጮች ዘገባ ሕዝቡ በተለይ በምስራቅ ሃረረጌ አወዳይ ከተማን ተቆጣጥሮ አደባባይ ወጥቷል::

በሁለቱ ከተሞች የፌደራል ፖሊስ በሕዝብ ላይ ባደረሰው ጥቃት 6 ሰዎች መሞታቸው ሲዘገብ ቁጥሩ ከዚህም በላይ ከፍ እንደሚል እየተገመተ ነው::
hareregeharerge
በሃሮማያ እና በአወዳይ እንደአዲስ በአገረሸው የሕዝብ ተቃውሞ; ሕዝቡ ወደከተማው የሚገቡና የሚወጡ መንገዶችን በተለይም ከሃረር እስከ ደንገጎ ያለውን መዝጋቱ ተሰምቷል:: በዚህ መንገድ የሚያልፉ መኪኖች መንገድ ስለተዘጋባቸው ወደ ጂጂጋ እና ድሬደዋ ለመመለስ መገደዳቸው ተዘግቧል::

No comments:

Post a Comment

wanted officials