Which one you first choose? በቅድሚያ የሚፈልጉት

Monday, December 7, 2015

የኦሮሞ ወጣቶችን ተቃውሞ በመጠቀም ገዢው መንግስት የኦሮሞን ሕዝብ ከሌላው ሕዝብ ለማጋጨት የሚያደርገውን ሴራ ሕዝቡ በንቃት እንዲመለከት ተጠየቀ


የኦሮሞ ወጣቶችን ተቃውሞ በመጠቀም ገዢው መንግስት የኦሮሞን ሕዝብ ከሌላው ሕዝብ ለማጋጨት የሚያደርገውን ሴራ ሕዝቡ በንቃት እንዲመለከት ተጠየቀ



(ዘ-ሐበሻ) የአዲስ አበባ ማስተር ፕላንን በመቃወም በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ ከተሞች እስከ ሰው ህይወት ማለፍን ያስተከተለ ተቃውሞ በመካሄድ ላይ መሆኑን ተክትሎ ገዢው መንግስት የተማሪዎቹን ጥያቄ የሃገር አንድነትን ከመበታተን ጋር በማያያዝ በብሔር ለመከፋፈል የሚያደርገውን ሴራ ሕዝቡ በንቃት እንዲከታተለው ተጠየቀ::



በተለያዩ የሶሻል ሚዲያዎች ላይ በተለይም የኦሮሞ ሕዝብ ደጋፊና ተቆርቋሪ በመምሰል ሰሞኑን ተማሪዎቹ እያደረጉ ያሉትን ተቃውሞ በመደግፍ ሌላውን ብሔር የመሳደብ እና የማጥላላት ዘመቻ መጀመሩን ተከትሎ ይህን የሚያደርጉት መንግስት ያሰማራቸው ካድሬዎች በመሆናቸው ሕዝቡ በንቃት እንዲከታተለው ተጠይቋል::

ከአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጋር በተያያዘ የተነሳውን ተቃውሞ እነዚሁ መንግስት ያሰማራቸው የሶሻል ሚዲያ ካድሬዎች ጥያቄው ወደ ሌላ ብሄር ጥላቻ እንዲሸጋገር በማደረግ ከፍተኛ ሥራ ላይ እንደተሰማሩ የታወቀ ሲሆን ይህም እንዲደረግ የተወሰነበት ምክንያት የኦሮሞ ተማሪዎች ጥያቄ የማስተር ፕላን ጥያቄ ሳይሆን የሌላ ብሄረሰብ ጥላቻ እንደሆነ ተደርጎ እንዲወሰድ ነው ተብሏል::

መንግስት የራሱ ን ካድሬዎች በማሰማራት በኦሮሞ ተወላጆች ስም ሆን ብሎ ሌላውን ብሄረሰብ በመሳደብ የተማሪዎቹን ጥያቄ ለማፈን የሚያደርገው ጥረት ከዚህ ቀደምም የተሞከረ እንደነበር ያስታወሱት የፖለቲካ ተንታኞች ባለፈው ዓመት በኦሮሚያ ክልል ውስጥ የሚገኙ የአማራ ተወላጅ ንብረት የሆነ ቤትን በማቃጠል እነዚሁ ለተቃውሞ የወጡ ሰዎች እንዳቃጠሉት በማስመሰል ለፕሮፓጋንዳና ለብሔር ግጭት የሚጋብዝ ሴራ ቢጠነሰስም ሕዝቡ የገዢው መንግስት ሴራ መሆኑን በመረዳት ማክሸፉ ይታወሳል::

በአንዳንድ የኦሮሚያ ክልሎች ተማሪዎቹ ሰላማዊ ጥያቄ ሲያቀርቡ በመሃላቸው መንግስት ያሰማራቸው ካድሬዎች ሕዝቡ ጋር በመመሳሰል ሌላውን ብሄር የሚሳደቡ መል ዕክቶችን አብረው እንዲናገሩ በማድረግ ሴራ ላይም የተሰማሩ እንዳሉ የጠቆሙት ተንታኞች ተማሪዎቹ ከእንደዚህ ያሉ ተኩላዎች መጠቀሚያ ሳይሆኑ በሰላማዊ መንገድ ሌላውን ሳይነኩ ጥያቄያቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሎ የፖለቲካ ተንታኞች ምክራቸውን ይለግሳሉ::

ከኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መስሪያ ቤት በሶሻል ሚድያዎች በተለይም በፌስቡክ በኦሮሞ ተወላጆች ስም ህዝብን ከሕዝብ የሚያቃቅሩ መል ዕክተኞች የተሰማሩ መሆኑን የሚጠቁሙት ምንጮች እነዚህ ሰዎች የሚያስተላልፏቸውንና ብሄርን ከብሄር ሊያጋጩ የሚችሉ መል ዕክቶችን በንቃት እንዲከታተሏቸው ተጠይቋል::

No comments:

Post a Comment

wanted officials